የ2013 ዓ.ም. 2ኛ ሳምንት አንኳር ወሬዎች

Ethiopia Zare's weekly news digest, week 2nd, 2013 Ethiopian calendar

የዓመቱ ሁለተኛ ሳምንት አንኳር ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ክንውኖች

ኢዛ (ከመስከረም 11 - 17 ቀን 2013 ዓ.ም.) ባሳለፍነው ሳምንት የተለያዩ ፖለቲካዊ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ክንውኖች ውስጥ የመከላከያ ሚኒስትሩ ምክትል ኤታማዦር ሹምና የፌደራል ፖሊስ ኮምሽነር ከወቅታዊ የአገሪቷ ሁኔታ አንጻር የሰጡት ተመሳሳይ ማስጠንቀቂያ ይጠቀሳል። ሁለቱም የአገሪቱ ከፍተኛ አመራሮችም የሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱ ውጭ የሚደረግ እንቅስቃሴን አንታገስም ብለዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በአልዩሚኒየም ፎይል ተጠቅልሎ ከአገር ሊወጣ የነበረ 132,860 ዶላር ኤርፖርት ላይ ተያዘ

በቦሌ ኤርፖርት ከአገር ሊወጣ የነበረው 132 ሺህ 860 ዶላር

ከአራት ነጥብ ስምንት ሚሊዮን ብር በላይ ነው

ኢዛ (እሁድ መስከረም ፲፯ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. September 27, 2020)፦ በአንድ የዚምባቡዌ ዜጋ ከአገር ሊወጣ የነበረ 132,860 ዶላር በአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት መያዙን የጉምሩክ ኮሚሽን አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የደመራ በዓል በአዲስ አበባና በተለያዩ የአገሪቱ ከተሞች እየተከበረ ይገኛል

የደመራ በዓል በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ ሲከበር

በመስቀል አደባባይ ከ5-6 ሺህ ታዳሚዎች ተገኝተዋል

ኢዛ (ቅዳሜ መስከረም ፲፮ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. September 26, 2020)፦ የመስቀል ደመራ በዓል በአዲስ አበባ ከተማ በመስቀል አደባባይ እየተከበረ ነው። ሐረርን ጨምሮ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች በዓሉ እየተከበረ ይገኛል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የ1954ቱ የወንጀለኛ መቅጫ ሕግ ሥነ ሥርዓት እንዲሻሻል የሚኒስትሮች ምክር ቤት ወሰነ

የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት

በሌሎች ጉዳዮችም ውሳኔ አሳልፏል

ኢዛ (ቅዳሜ መስከረም ፲፮ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. September 26, 2020)፦ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ቅዳሜ መስከረም 16 ቀን 2013 ዓ.ም. ባካሔደው 90ኛ መደበኛ ስብሰባው፤ የ1954ቱን የኢትዮጵያ የወንጀለኛ መቅጫ ሕግ ሥነ ሥርዓት እና የማስረጃ ረቂቅ አዋጅ ላይ ማሻሻያ እንዲደረግ ውሳኔ አሳለፈ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአርቲስት ሐጫሉን ግድያ ተከትሎ በተፈጸሙ ወንጀሎች ምርመራ ተጠናቀቀ

Fekadu Tsega (L) and Husen Osman (R)

የፌዴራልና የኦሮሚያ ዓቃቤ ሕጎች በ5,728 ግለሰቦች ላይ ክስ መመሥረታቸው ተገለጸ
በኹከቱ የወደመ ንብረት 4.7 ቢሊዮን ብር ነው
በሐረር ሐውልት ያፈረሱ በሽብር ሕጉ ይጠየቃሉ

ኢዛ (ቅዳሜ መስከረም ፲፮ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. September 26, 2020)፦ ከአርቲስት ሐጫሉ ሁንዴሳ ግድያን ተከትሎ በተፈጸሙ ወንጀሎች ዙሪያ በኦሮሚያ ክልል ሲያካሒድ የነበረውን ምርመራ ዓቃቤ ሕግ ማጠናቀቁንና በወቅቱ በተፈጸሙ ጥቃቶች 4.67 ቢሊዮን ብር ግምት ያለው ንብረት መውደሙን ገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የመስቀልና የኢሬቻ በዓላት ላይ ሽብር ለመፍጠር ዝግጅት እንደነበር ተገለጸ

Commissioner General Endeshaw Tasew

ፖሊስ በሁሉም የአዲስ አበባ መግቢያዎች ጥበት ቁጥጥር እየተደረገ ነው
ፖሊስ ከመስከረም 25 በኋላ መንግሥት የለም የሚሉት ላይ እርምጃ እወስዳለሁ አለ

ኢዛ (ዓርብ መስከረም ፲፭ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. September 25, 2020)፦ ፌዴራል ፖሊስ በአራቱም የአዲስ አበባ መግቢያ በሮ ጥብቅ ፍተሻ እያካሔደ መኾኑንና በአዲስ አበባ የሽብር ድርጊት ለመፈጸም ዝግጅት ላይ እንዳሉ እንደደረሰበትም አስታውቋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አርቲስት አልማዝ ኃይሌ አረፈች

Almaz Haile

ሥርዓተ ቀብሯ ነገ ይፈጸማል

ኢዛ (ዓርብ መስከረም ፲፭ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. September 25, 2020)፦ ከ42 ዓመታት በላይ በሞያዋ መልካም ሥም ያተረፈችው ታዋቂዋ አርቲስት አልማዝ ኃይሌ ዛሬ ዓርብ መስከረም 15 ቀን 2013 ዓ.ም. ከዚህ ዓለም በሞት ተለየች። ባለፈው መስከረም 1 ቀን 2013 ዓ.ም. የ75ኛ ዓመት የልደት በዓልዋ ተከብሮላት ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በቤንሻንጉል ጉሙዝ በዳግመኛ ጥቃት የንጹኀን ሕይወት አለፈ

Benishangul Gumuz

የሰብአዊ መብት ኮሚሽን 15 ሰዎች መገደላቸውን አረጋግጫለሁ አለ

ኢዛ (ዓርብ መስከረም ፲፭ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. September 25, 2020)፦ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን፣ ዳንጉር ወረዳ፣ ማንቡክ ከተማ በንገዝ ወንዝ አካባቢ በሚገኝ መንደር ዛሬ ከንጋቱ 10 ሰዓት አካባቢ ዳግመኛ ጥቃት ተሰንዝሮ ከ15 - 20 የሚኾኑ ንጹኀን ሕይወታቸው መቀጠፉ ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

እነአቶ ጃዋር መሐመድ ከዛሬ ጀምሮ ወደ ማረሚያ ቤት እንዲሔዱ ትእዛዝ ተሰጠ

Jawar Mohammed (L), Bekele Gerba (R)

ጠበቆች ማረሚያ ቤት አይውረዱ ብለው ተከራክረው ነበር

ኢዛ (ሐሙስ መስከረም ፲፬ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. September 24, 2020)፦ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በእነአቶ ጃዋር መሐመድ ላይ የተመሠረተባቸውን ክስ ለመስማት ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጠ። በዚህ መዝገብ የተከሰሱ ግለሰቦች ጉዳያቸውን በማረሚያ ቤት ኾነው እንዲከታተሉም ታዝዟል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የምክትል ኤታማዦር ሹሙ ማስጠንቀቂያ

Gen. Berhanu Julla

በኃይል ፍላጎቴን አሳካለሁ በሚል ማናቸውም አካል ላይ እርምጃ ለመውሰድ እንገደዳለን አሉ

ኢዛ (ሐሙስ መስከረም ፲፬ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. September 24, 2020)፦ ሕገ መንግሥቱን በጣሰ መልኩ በኃይል ፍላጎቴን አሳካለሁ በሚል የትኛውም አካል ላይ እርምጃ ለመውሰድ የሚገደዱ መኾናቸውን ምክትል ጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙ ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ አስታወቁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ