ፕሮፌሰር መስፍን በክብር ተሸኙ

Prof. Mesfin WoldeMariam's funeral

ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናትና ታዋቂ ሰዎች ተገኝተዋል

ኢዛ (ማክሰኞ መስከረም ፳፮ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. October 6, 2020)፦ የእውቁ ምሁርና የሰብአዊ መብት ተሟጋቹ የፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም ሥርዓተ ቀብር ዛሬ ማክሰኞ መስከረም 26 ቀን 2013 ዓ.ም. በክብር ተፈጽሟል። ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናትና ታዋቂ ሰዎች ተገኝተዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የፌዴራል መንግሥት ከትግራይ ክልል ምክር ቤት ጋር ግንኙነት አቋረጠ

House of Federation and TPLF

የፌዴራል መንግሥቱ ከከተማና ከቀበሌ አስተዳደሮችና ሕጋዊ ተቋማት ጋር ብቻ ግንኙነት ያደርጋል

ኢዛ (ማክሰኞ መስከረም ፳፮ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. October 6, 2020)፦ የፌዴራል መንግሥት ከትግራይ ክልል ምክር ቤት እና ከፍተኛ የሕግ አስፈጻሚ አካል ግር ምንም ዐይነት ግንኙነት ማድረግ እንደማይችል የፌዴሬሽን ምክር ቤት ዛሬ መስከረም 26 ቀን 2013 ዓ.ም. ወሰነ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሕወሓት በአመራር ላይ ያሉ አባላቱን ኃላፊነታቸውን ለቅቃችሁ ሪፖርት አድርጉ አለ

TPLF letter to Dr. Arkebe Oqubay

ለ27ቱ የሕወሓት የፓርላማ አባላትም ተመሳሳይ ጥሪ አስተላልፏል

ኢዛ (ሰኞ መስከረም ፳፭ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. October 5, 2020)፦ ሕወሓት በፌዴራል ደረጃ በተለያዩ የአመራር ደረጃ ለሚገኙ 13 አባላቱና በፓርላማ የድርጅቱ አባል ናቸው ላላቸው 27 የፓርላማ አባላቱ፤ ኃላፊነታችሁን አቁማችሁ ለድርጅታችሁ ሪፖርት እንድታደርጉ ሲል ጥሪ አስተላለፈ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢትዮጵያ በታላቁ ህዳሴ አካባቢ የሲቪልም ኾነ ወታደራዊ በረራዎችን ከለከለች

Grand Ethiopian renaissance dam

በዚያ አካባቢ ለመብረር ልዩ ፈቃድ መሰጠት እንዳለበት ተገልጿል
የመንግሥት እርምጃ የህዳሴውን ግድብ ድኅንነት ለመጠበቅ ነው

ኢዛ (ሰኞ መስከረም ፳፭ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. October 5, 2020)፦ የታላቁ ህዳሴ ግድብ በሚገኝበት የአየር ክልል፤ ከተፈቀደላቸው በረራዎች ውጭ ማንኛውም የሲቪልም ኾነ ወታደራዊ በረራዎች ዝግ መደረጉና መከልከሉ ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የፕሮፌሰር መስፍን ሥርዓተ ቀብር ነገ ይፈጸማል

Prof. Mesfin WoldeMariam

ከቀብር ሥነ ሥርዓቱ በፊት የሻማ ማብራትና የሽኝት ፕሮግራም ይካሔዳል

ኢዛ (ሰኞ መስከረም ፳፭ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. October 5, 2020)፦ የፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም የቀብር ሥነ ሥርዓት ነገ ማክሰኞ መስከረም 26 ቀን 2013 ዓ.ም. በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ቤተ ክርስቲያን ይፈጸማል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ተጠባቂው የሁለቱ ምክር ቤቶች ስብሰባ ዛሬ ከሰዓት በኋላ ይካሔዳል

TPLF

የሕወሓት አባላት ይገኛሉ ወይስ አይገኙም የሚለው በጉጉት እየተጠበቀ ነው

ኢዛ (ሰኞ መስከረም ፳፭ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. October 5, 2020)፦ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና የፌዴሬሽን ምክር ቤት የጋራ ስብሰባቸውን ዛሬ ሰኞ መስከረም 25 ቀን 2013 ዓ.ም. ከቀትር በኋላ ያካሒዳሉ። የሕወሓት የሁለቱም ምክር ቤቶች አባላት በስብሰባው ላይ ይገኛሉ ወይስ አይገኙም የሚለው በጉጉት እየተጠበቀ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኢሬቻን በዓል በሰላም እንዳይካሔድ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ከ500 በላይ ሰዎች ተያዙ

ኢሬቻ፣ Irrecha

ፖሊስ ባደረገው ክትትል 14 ክላሽ 26 የእጅ ቦንብና 103 ሽጉጦችን መያዙን ገለጸ
በዓሉን የሚከብሩት ከስድስት ሺህ የማይበልጡ ታዳሚዎች ናቸው

ኢዛ (ዓርብ መስከረም ፳፪ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. October 2, 2020)፦ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ፖሊስ መስከረም 23 እና 24 ዓ.ም. የሚከበረው የኢሬቻ በዓል በሰላማዊ መንገድ እንዳይካሔድ ሲንቀሳቀሱ ነበር ያላቸውን ከ500 በላይ ግለሰቦችን በቁጥጥር ሥር ማዋሉንና የጦር መሣሪያዎችን መያዙን አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ፕሮፌሰር መስፍን በሰብአዊ መብት ተሟጋችነታቸው በታሪክ የሚታወሱ መኾኑን ኢሰመኮ ገለጸ

ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም (በግራ)፣ ኢሰመኮ (መኻል)፣ ዶ/ር ዳንኤል በቀለ (በቀኝ)

“ፈር ቀዳጅ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ነበሩ” ኢሰመኮ

ኢዛ (ዓርብ መስከረም ፳፪ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. October 2, 2020)፦ ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም በኢትዮጵያ ካሉት ታላቅ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ኾነው በታሪክ ሲታወሱ እንደሚኖሩ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የፕሮፌሰር መስፍን ሥርዓተ ቀብር በሚቀጥለው ሳምንት ይፈጸማል

Prof. Mesfin WoldeMariam

እንደ አንድ ታላቅ ኢትዮጵያዊ በክብር ሥርዓተ ቀብራቸው እንዲፈጸም ለቀረበው ጥያቄ ምላሽ እየተጠበቀ ነው

ኢዛ (ዓርብ መስከረም ፳፪ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. October 2, 2020)፦ እውቁ የሰብአዊ መብት ተሟጋችና ምሁር ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም ሥርዓተ ቀብር በሚቀጥለው ሳምንት እንደሚፈጸም ተጠቆመ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ