ዛሬ ሦስት ሰዎች በኮሮና መያዛቸው ይፋ ኾነ

Total Coronavirus Cases in Ethiopia

በአገሪቱ በበሽታው የተያዙት ቁጥር 194 ደረሰ

ኢዛ (ዓርብ ሚያዝያ ፴ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. May 8, 2020)፦ ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ የኮሮና ቫይረስ ምርመራ ከተደረገላቸው 1,861 ሰዎች ውስጥ ሦስት በቫይረሱ የተጠቁ አዳዲስ ሰዎች መገኘታቸውን የጤና ሚኒስቴር ዛሬ ይፋ አደረገ። በአገሪቱ በበሽታው የተያዙት ቁጥር 194 ደርሷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አቶ በረከት የስድስት ዓመት፣ አቶ ታደሰ ደግሞ የስምንት ዓመት እስራት ተፈረደባቸው

Bereket Simon and Tadese Kassa

የፍርድ ቤቱ በገንዘብም እንዲቀጡ ወስኗል

ኢዛ (ዓርብ ሚያዝያ ፴ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. May 8, 2020)፦ በእነአቶ በረከት ስምኦን የክስ መዝገብ ሲመለከት የነበረው የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት፤ ዛሬ ዓርብ ሚያዝያ 30 ቀን ከእነአቶ በረከት ስምኦን ላይ የስድስት ዓመት እስር ሲፈርድ፤ በአቶ ታደሰ ካሣ ላይ ደግሞ የስምንት ዓመት የእስር ፍርድ ወሰነባቸው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሚኒስትሮች ምክር ቤት የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳለፈ

Office of the Prime Minister, Ethiopia

የወንጌላውያን ካውንስል ሕጋዊነትን የሚያረጋግጥ አዋጅ ይጽደቅ ብሏል
የልማት ባንክን የማቋቋሚያ ስዋጅ እንዲሻሻል ወስኗል

ኢዛ (ሐሙስ ሚያዝያ ፳፱ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. May 7, 2020)፦ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ሐሙስ ሚያዝያ 29 ቀን 2012 ዓ.ም. ባካሔደው ሃያኛው አስቸኳይ ስብሰባ የኢትዮጵያ ልማት ባንክን ማቋቋሚያ ደንብ እንዲሻሻል ውሳኔ ሲያሳልፍ፤ በተመሳሳይ የኢትዮጵያ ወንጌላዊያን አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ሕጋዊ ሰውነት ለመስጠት የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ እንዲጸድቅ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መርቷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አብን የሽግግር መንግሥት መፍትሔ አለመኾኑን ገለጸ

አብን

ምርጫ እስኪደረግ አሁን ያለው መንግሥት መቀጠሉ አንጻራዊ መፍትሔ ነው ብሏል

ኢዛ (ሐሙስ ሚያዝያ ፳፱ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. May 7, 2020)፦ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ኢትዮጵያ አሁን ለገባችበት ፖለቲካዊ ቀውስ አዲስ የሽግግር መንግሥት መፍትሔ ይኾናል የሚል እምነት እንደሌለው አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሕገ መንግሥቱ ውጪ በሚንቀሳቀሱ አካላት ላይ እርምጃ እንደሚወስዱ አስታወቁ

PM Abiy Ahmed saluting

የኮሮና ቫይረስ እስኪወገድና ምርጫ እስኪደረግ አገር የማስተዳደሩ ኃላፊነት የብልጽግና መኾኑንም ገልጸዋል

ኢዛ (ሐሙስ ሚያዝያ ፳፱ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. May 7, 2020)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ የአገርንና የሕዝብን ደኅንነት ለመጠበቅ ሲል ሕገ መንግሥቱን የሚጥሱ ሕገ ወጥ እንቅስቃሴዎች ላይ እርምጃዎችን ለመውሰድ የሚገደድ መኾኑን አስታወቁ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን የገለጹት በወቅታዊ አገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ዛሬ ሐሙስ ሚያዝያ 29 ቀን 2012 ዓ.ም. ባስተላለፉት መልእክት ላይ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በትግራይ ክልል አራት የኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎች ተገኙ

This illustration, created at the Centers for Disease Control and Prevention (CDC)

ይህም በአንድ ቀን ቫይረሱ የተገኘባቸውን 29 አድርሶታል

ኢዛ (ሐሙስ ሚያዝያ ፳፱ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. May 7, 2020)፦ በዛሬው ዕለት የኮሮና ቫይረስ ከተገኘባቸው 25 ግለሰቦች በተጨማሪ፤ በትግራይ ክልልም አራት በቫይረሱ የተጠቁ ሰዎች መገኘታቸውን የትግራይ ጤና ቢሮ በማስታወቁ፤ ባለፉት 24 ሰዓታት በኢትዮጵያ በቫይረሱ የተጠቁ ሰዎች ቁጥር 29 መድረሱ ታውቋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ብዙዎችን ያስደነገጠው ሪፖርት

3ዲ (3D) ኮሮና ቫይረስ በምስል (© istock.com/Dr_Microbe)

በ24 ሰዓት ውስጥ 25 የኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎች ተገኙ

ኢዛ (ሐሙስ ሚያዝያ ፳፱ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. May 7, 2020)፦ የኮሮና ቫይረስ በኢትዮጵያ መከሰቱ ከተገለጸበት መጋቢት 4 ቀን 2012 ዓ.ም. ወዲህ በብዙዎች ዘንድ ድንጋጤ የፈጠረው ዛሬ የተደረገው ሪፖርት ነው ማለት ይቻላል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢዜማ በወቅታዊ አገራዊ ጉዳይ ላይ ያለውን አቋም የሚገልጽ መግለጫ አወጣ

ኢዜማ

ፓርቲው በኢፌዴሪ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 104 እና 105/2 መሠረት የሕገ መንግሥት ማሻሻያ ማድረግ የሚል አማራጭ ሐሳብ ላይ ተስማምቷል

ኢዛ (ረቡዕ ሚያዝያ ፳፰ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. May 6, 2020)፦ ኢዜማ (የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ ፓርቲ) ከወቅታዊ የአገሪቱ ሁኔታ ጋር በተያያዘ የፓርቲውን አቋምና መኾን ይገባዋል ብሎ የሚያምንባቸውን እርምጃዎች የሚያመለክት መግለጫ ዛሬ አውጥቷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በታላቁ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ ግብጽ ለተመድ አቤቱታ አቀረበች

Grand Ethiopian renaissance dam

ኢትዮጵያ በአቋሜ እንደጸናሁ ነው ብላለች

ኢዛ (ረቡዕ ሚያዝያ ፳፰ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. May 6, 2020)፦ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ሙሌትን በተመለከተ ግብጽ ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አቤቱታ ያቀረበች ሲሆን፤ ኢትዮጵያ አቤቱታው የሚለውጠው ነገር አለመኖሩን ገልጻለች።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የፊታችን ዓርብ በነአቶ በረከት ላይ የቅጣት ውሳኔ ይተላለፋል ተብሎ ይጠበቃል

Bereket Simon and Tadese Kassa

ፍርድ ቤቱ በዛሬው ችሎት የተከሳሾችን የቅጣት ማቅለያና የዓቃቤ ሕግን የቅጣት ማክበጃ አድምጧል

ኢዛ (ረቡዕ ሚያዝያ ፳፰ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. May 6, 2020)፦ በእነአቶ በረከት ስምኦን የክስ መዝገብ የጥፋተኝነት ውሳኔ ያስተላለፈው የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት፤ ዛሬ ረቡዕ ሚያዝያ 28 ቀን ከእነአቶ በረከትና ከዓቃቤ ሕግ የቅጣት አስተያየት ካዳመጠ በኋላ፤ የቅጣት ውሳኔ ለማስተላለፍ ለዓርብ ሚያዝያ 30 ቀን 2012 ዓ.ም. ቀጠሮ ሰጠ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ