የግል እጩ ተወዳዳሪዎች 50 ሺህ ብር ውሰዱ ተባሉ

Ethiopian Election 2021

7.4 ሚሊዮን ብር ለግል ተወዳዳሪዎች ሊሰጥ ነው

ኢዛ (ረቡዕ ሰኔ ፱ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. June 16, 2021)፦ በዘንድሮው ምርጫ 2013 በግል ተወዳዳሪ የኾኑ እጩዎች ለእያንዳንዳቸው 50 ሺህ ብር የገንዘብ ድጋፍ እንዲደረግላቸው መወሰኑን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታውቋል። በዘንድሮው ምርጫ በግል ለመወዳደር የተመዘገቡት እጩዎች 148 ናቸው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በመጨረሻው የቅስቀሳ ቀን

PM Abiy Ahmed

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለምርጫ ቅስቀሳ ወደ ትውልድ መንደራቸው ሔዱ

ኢዛ (ረቡዕ ሰኔ ፱ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. June 16, 2021)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ወደ ትውልድ ቀያቸው የምረጡኝ ቅስቀሳ ለማድረግ ጅማ ከተማ ገብተዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የፓርቲዎች የምርጫ ቅስቀሳ ዛሬ ያበቃል

Ethiopian Election 2021

አንዳንድ የአዲስ አበባ መንገዶች ዝግ ይኾናሉ

ኢዛ (ረቡዕ ሰኔ ፱ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. June 16, 2021)፦ የፖለቲካ ፓርቲዎች ለስድስተኛው አገራዊ ምርጫ 2013 ሲያካሒዱ የቆዩት ቅስቀሳ በዛሬው ዕለት (ረቡዕ ሰኔ 9 ቀን 2013 ዓ.ም.) የሚጠቃለል ሲሆን፤ በዚህም ምክንያት በአዲስ አበባ አንዳንድ የአዲስ አበባ መንገዶች ለአገልግሎት ዝግ ይኾናሉ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ምርጫ ቦርድ ሰኔ 14 የመንግሥትና የግል ተቋማት ሥራ ዝግ እንደሚኾን አስታወቀ

Ethiopian Election 2021

ሐረሪ እና ሶማሌ ክልልን አይመለከትም

ኢዛ (ማክሰኞ ሰኔ ፰ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. June 15, 2021)፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም. በሚካሔደው ስድስተኛው አገራዊ ምርጫ መንግሥታዊ እና መንግሥታዊ ያልኾኑ ተቋማት በዕለቱ ሥራቸው ዝግ እንደሚኾን አስታወቀ። ሐረሪ እና ሶማሌ ክልልን አይመለከትም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ምክር ቤቱ ከግማሽ ትሪሊዮን ብር በላይ ረቂቅ በጀት ላይ ዛሬ መክሮ በጀቱን ያጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል

Ethiopian Parliament Building

ለመከላከያ ስድስት ቢሊዮን ብር ለ2013 ተጨማሪ በጀት ተመድቦ ነበር
የ2014 የአገሪቱ በጀት ከአምናው 59.3 ቢሊዮን ብር ብልጫ አለው

ኢዛ (ማክሰኞ ሰኔ ፰ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. June 15, 2021)፦ የሚኒስትሮች ምክር ቤት የፌዴራል መንግሥት የ2014 በጀት ዓመት የአገሪቱ በጀት ከግማሽ ትሪሊዮን ብር በላይ እንዲኾን ውሳኔ ያሳለፈበትን ረቂቅ በጀት ላይ፤ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ይወያይበታል። በጀቱንም ያጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ከምርጫ 2013 እጩ ተወዳዳሪዎች ራሳቸውን ማግለል ጀመሩ

Ahmedin Jebele

በመጨረሻው ሰዓት ኡስታዝ አሕመዲን ራሱን ከምርጫ አገለለ

ኢዛ (ሰኞ ሰኔ ፯ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. June 14, 2021)፦ አንድ ሳምንት በቀረው ስድስተኛው አገራዊ ምርጫ (ምርጫ 2013) ላይ በግል እንደሚወዳደሩ ካሳወቁት ታዋቂ ግለሰቦች መካከል የሚጠቀሱት ኡስታዝ አሕመዲን ጀበል ከምርጫው ራሱን እንዳገለለ አስታወቀ። እስካሁን ከምርጫውን ራሳቸው በኦፊሴል ያገለሉ እጩ ተወዳዳሪዎች ባላመኖራቸው፤ ኡስታዝ አሕመዲን ጀበል የመጀመሪያው እጩ ተወዳዳሪ ኾኗል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

“እጃችሁን አንሱ!” በአዲስ አበባ

Hands off Ethiopia

የአሜሪካና የምዕራባውን አገሮች በኢትዮጵያ ላይ የሚደርጉትን ጣልቃ ገብነት ኢትዮጵያውያን ተቃወሙ

ኢዛ (ዓርብ ግንቦት ፲፫ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. May 21, 2021)፦ አሜሪካ እና ምዕራባውያን አገሮች በኢትዮጵያ ላይ እያራመዱ ያሉትን ጣልቃ ገብነት በመቃወም ኢትዮጵያውያን የተቃውሞ ድምፃቸውን አሰምተዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአሜሪካ በትር

USA and Ethiopian flags

አሜሪካ ኢትዮጵያ ላይ ማእቀብ ለመጣል እየተዘጋጀች ነው

ኢዛ (ዓርብ ግንቦት ፲፫ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. May 21, 2021)፦ የአሜሪካ መንግሥት በኢትዮጵያ ላይ በትር ለማሳረፍ የጀመረችውን ጫና ያጠናክርልኛል ያለችውን ማእቀብ ለመጣል እየተዘጋጀች ስለመኾኑ እየተሰማ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በብልጽግና የድጋፍ ሰልፍ ላይ በተፈጠረ ግጭት ሕይወት ጠፋ

National Movement of Amhara (NAMA) and Prosperity party

መንግሥት ለጥቃቱ ትእዛዝ የሰጡና የፈጸሙ አካላት ላይ አስቸኳይ ምርመራ በማድረግ ሕጋዊ እርምጃ እንዲወሰድና ውጤቱን ለሕዝብ ይፋ እንዲያደርግ አብን ጠይቋል

ኢዛ (ዓርብ ግንቦት ፲፫ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. May 21, 2021)፦ በአማራ ክልላዊ መንግሥት በምዕራብ ጎጃም ዞን መርአዊ ከተማ የብልጽግና ፓርቲ በጠራው የድጋፍና የምርጫ ቅስቀሳ ሰልፍ ላይ በተፈጠረ ግጭት ሁለት ተማሪዎች ሲሞቱ 12 የሚኾኑ መቁሰላቸው ተሰማ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ምርጫ 2013 ሰኔ 14 እንደሚካሔድ ተገለጸ

National Election Board of Ethiopia (NEBE)

• በሐረር እና በሱማሌ ክልሎች ሰኔ 14 ምርጫው አይካሔድም

• በምርጫ ምዝገባ አቤቱታ የቀረበባቸው የምርጫ ክልሎች ምርጫው በዕለቱ አይካሔድም

ኢዛ (ሐሙስ ግንቦት ፲፪ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. May 20, 2021)፦ ስድስተኛው አገራዊ ምርጫ 2013 ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም. እንደሚካሔድና የምርጫ ሒደቱም የመራጮች ምዝገባ በተጠናቀቀባቸው ቦታዎች ብቻ እንደሚካሔድ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ በሰጠው መግለጫ አስታውቋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ