የተያዘው ሥራ ህዝብን ማስተባበር ወይንስ ከትግሉ ፈጽሞ ማራቅ
ፍቅሩ ይበልጣል
ሰሞኑን በሀገራችን ፖለቲካ ለሁለተኛ ጊዜ የህዝብን ቅስም የሚሰብር ድርጊት በመካሄድ ላይ ይገኛል። በአንድ ወቅት የህዝብን የጋለ ስሜት አነሳስቶ የነበረውና ወደ ድል ሊያሸጋግረው ነበረው የቀድሞው ቅንጅት፣ በአመራር ላይ ባሉ ግለሰቦች አሳፋሪ የሆነ ድክመት ባልታሰበና ህዝብና ደጋፊ ባልጠበቀው ሁኔታ መንገድ ስቶ ተንኮታኩቶ ወደቀ። ያንን የወዳደቀ ስብርባሪውን አንስተው፣ ጠግነው፣ የተሰበረውን የህዝብ ልብ መልሰን ቀድሞ ወደነበረው አመኔታ እንመልሰዋለን በማለት የተነሱ ጥቂት አመራሮች እንደገና በማንሰራራት የቅንጅት ወራሽ የሆነውን አንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ በሚል ስያሜ በመመስረትና ልበ ሙሉዋን ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳን በመሪነት በመምረጥ ትግሉን ለመቀጠል ለህዝብ ቃል ገቡ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...

(ስለ ኃይሉ፣ ኢህአዴግ፣ ፈረንጆቹና ብርቱካን) 


