የኢትዮጵያንና የኤርትራን ሕዝብ የሚያስተሳሥሩ ቋሚ ሠንሰለቶች (ፕ/ር ዳንኤል ክንዴ)

ፕሮፌሠር ዳንኤል ክንዴ ከማርች 25 እስከ 27 ቀን 2011 እ.ኤ.አ. በካሊፎርኒያ ሳንሆዜ በተካሄደው በሦስተኛው የኢትዮጵያና የኤርትራ ወዳጅነት ጉባዔ ላይ ”የኢትዮጵያንና የኤርትራን ሕዝብ የሚያስተሳስሩ ቋሚ ሠንሰለቶች” በሚል ርዕስ ጥናታዊ ጽሑፍ አቅርበው ነበር። ይህንን ጥናታዊ ጽሑፉ ለኢትዮጵያ ዛሬ ድረ ገጽ የላኩልን ሲሆን፣ በዚህ አጋጣሚ ምስጋናችንን ለፕ/ር ዳንኤል እያቀረብን፤ ምንም ሳንጨምርና ሳንቀንስ እንደወረደ አቅርበነዋል። መልካም ንባብ!! 

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የፓርላማው አባላት ያጨበጨቡት ለምንድነው?

ታደሰ ብሩ

ይህንን ዜና ምን ትሉታላችሁ?

ዋናው ኦዲተር የፓርላማ አባላትን ያስጨበጨበ ሪፖርት አቀረበ

የፌዴራል ዋና ኦዲተር፣ ዛሬ ለተወካዮች ምክር ቤት ያቀረበው የፌዴራል መንግሥት መሥርያ ቤቶች የ2002 በጀት ዓመት ሒሳብ ኦዲት ሪፖርት የፓርላማ አባላትን አስጨበጨበ። በርካታ የመንግሥት መ/ቤቶች የአፈጻጸም ጉድለቶችን ፈጽመዋል። ሪፖርተር ጋዜጣ ሰኔ 1 ቀን 2003 ዓ.ም.

ለምንድነው የፓርላማ አባላቱ ያጨበጨቡት? የኦዲተሩ ሪፖርቱ ምን አስደናቂ ነገር ይዟል? ቀጥለን ያለውን አንቀጽ እናንብብ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኮሎኔል ተስፋዬ ወልደሥላሴ ሞት

እስክንድር ነጋ (አዲስ አበባ)

የደርግ የቀድሞ የደህንነት ሚኒስትር፣ ኮሎኔል ተስፋዬ ወልደሥላሴ፣ ባለፈው ቅዳሜ፣ ግንቦት 27 ቀን 2003 ዓ.ም.፣ በእስር ላይ በነበሩበት ቃሊቲ ወህኒ ቤት አርፈዋል። ወንዳወንድ ገፅታና ደንዳና ሰውነት የነበራቸው ኮ/ል ተስፋዬ፣ በሕይወት ዘመናቸው ብዙ ከመናገር ይልቅ ማዳመጥን የሚወዱ ሰው እንደነበሩ በቅርብ የሚያውቋቸው ሰዎች ይናገሩላቸዋል። የደርግ አባል አልነበሩም። ሆኖም፣ አብዮቱ የመጣላቸው እንጂ የመጣባቸው እንዳልነበር ነጋሪ አላስፈለጋቸውም። ተስፋዬ የጭቁኖች ልጅ ነበሩ። ወዲያው ነበር ታማኝ የሆኑት። 

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የተደበቁ እውነቶች በሳውዲ አረቢያ (ክፍል አስር - ነብዩ ሲራክ)

(ነብዩ ሲራክ - ከሳውዲ አረቢያ)

ካጠፋነው እንማር በበጎ እንበረታበት ዘንድ ያለፈውን ዛሬ ላይ እያነሳሁ በማዘክርበት ቀጣይ መጣጥፌ በሳውዲ የተለያዩ እስር ቤቶች ስቃይ መከራቸውን ስለሚያዩ ወገኖች፣ በቆንስሉ ግቢ በሚገኘው መጠለያ ስለሚገኙ ወገኖችና አልፎ አልፎ በሰሞኑ ሰበር ወጋወጌ ያየሁ የሰማሁትን በመረጃ እየደገፍኩ ለማቅረብ ሙከራ ማድረጉን ገፍቸበታለሁ። (ሙሉውን ጽሑፍ በፒ.ዲ.ኤፍ. አስነብበኝ!

የመሬት ንጥቂያውና የወደፊቱ መከራችን

ሉሉ ከበደ (ካናዳ)

      

ቀደምት የሐገራችን አንባገነኖች ሕዝባችንን ሲገሉና ሲያስሩ ሲያሰቃዩ የነበረው  ባብዛኛው ስልጣናቸውን ለመጠበቅ ሲሉ መሆኑ ብዙም የሚያከራክረን አይደለም።  አሁን ያሉት ግን ለስልጣንም፤ ለገንዘብ፤ ለሐብትም ሖኗል። የኢትዮጵያ ሕዝብ እንዳለፉት ሀያ ዓመታት መብቱ ተገፎ፤ ሰብእናው ተረግጦ፤ ተከፋፍሎ፤ ታስሮ፤ ተገሎ፤ ተዘርፎ፤ ለህይወቱና ለንብረቱ፤ ለስራው፤ ለኑሮው ዋስትና አጥቶ፣ ፈርቶ፤ ተጨንቆእንዲኖር የተደረገበት ዘመን ቢኖር አሁን ነው። ሙሉውን አስነብበኝ ...

የመሬት ንጥቂያውና የወደፊቱ መከራችን

ሉሉ ከበደ (ካናዳ)

ቀደምት የሐገራችን አንባገነኖች ሕዝባችንን ሲገሉና ሲያስሩ ሲያሰቃዩ የነበረው ባብዛኛው ስልጣናቸውን ለመጠበቅ ሲሉ መሆኑ ብዙም የሚያከራክረን አይደለም። አሁን ያሉት ግን ለስልጣንም፤ ለገንዘብ፤ ለሐብትም ሖኗል። የኢትዮጵያ ሕዝብ እንዳለፉት ሀያ ዓመታት መብቱ ተገፎ፤ ሰብእናው ተረግጦ፤ ተከፋፍሎ፤ ታስሮ፤ ተገሎ፤ ተዘርፎ፤ ለህይወቱና ለንብረቱ፤ ለስራው፤ ለኑሮው ዋስትና አጥቶ፣ ፈርቶ፤ ተጨንቆ፤ እንዲኖር የተደረገበት ዘመን ቢኖር አሁን ነው። 

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ግንቦት 20 እና የጠፋው 8.5 ቢሊዮን ዶላር

እስክንድር ነጋ (አዲስ አበባ)

(ክፍል ሁለት - ካለፈው ሣምንት የቀጠለ)

ቅዳሜ ረፋዱ ላይ ጀምበር ለመጥለቅ ዳር ዳር ትላለች። የግንቦት አናት ሰርሳሪ ፀሐይ ዘንድሮ በደመና ለዝቦ ነው የሰነበተው። ከእኩለ ቀን አንስቶ የከተማዋ አየር ቀዝቀዝ ብሎ ውሏል። አንዳንዴም መለስተኛ ካፊያ መጠት ሄደት ይላል። 

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢትዮጵያና የጠፋው 8.5 ቢሊዮን ዶላሯ

እስክንድር ነጋ (አዲስ አበባ)

ክፍል አንድ

ትላንት፣ እሁድ፣ ግንቦት 14'2003 ዓ.ም፣ የእናቴን አርባ አወጣኹ። ውስጤ የፈጠረውን ስሜት ልገልፀው አልችልም። ደስታ አይደለም። በውስጤ ያለው ባዶነት ደስታን ውጦ የሚያስቀር ጨለማ ጉድጓድ ነው። እርካታ ብለው የተሻለ ይመስለኛል። የእናቴ ነፍስ ከእንግዲህ የፍርድ ቀንን በሰላም መጠበቅ ትችላለች ብዬ አስባለኹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የ… ዕድር አባላት አስቸኳይ ስብሰባ

ነፃነት ዘገዬ This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.

"… የምግብ ዘይት እንኩዋን በአቅሟ ሜርኩሪ ስትሆን ምን ይዋጠን? በደርግ ጊዜ በሊትር ሦስትና አራት ብር ትሸጥ የነበረች ከምን እንደተሠራች እንኳን በውል የማትታወቅ አንዲት ሊትር ተራ ዘይት ዛሬ በነፃ አውጫችን በጎብላላው ኢህአዴግ ዘመን ሰባ ብር ላይ ወጥታ ቂብ ስትል ምን ይባላል? በ‘ጨቁዋኙና ሰው በላው’ የቀዳማዊ ኃ/ሥላሴ ዘመነ መንግሥት በሃያ ሣንቲም ይገዛ የነበረ ማለፊያ ጠረን ያለው አንድ የጣሊያን የልብስ ሣሙና ዛሬ በ28 ብር ሲገዛ የፀሐዩን መንግሥታችንን የኢሕአዲግን ዕድሜ ያርዝምልን ከማለት ውጪ ምን እንላለን? …" 

ሙሉውን አስነብበኝ ...