የነፃው ፕሬስ አሣታሚ ድርጅቶች ለፍ/ቤት ተቃውሟቸውን አቀረቡ
Ethiopia Zare (ዓርብ ታህሳስ 17 ቀን 2001 ዓ.ም. December 26, 2008)፦ “ሕገ መንግሥታዊውን ሥርዓት በኃይል ለመናድ” በሚል፣ በእነ ኢንጂንየር ኃይሉ ሻውል የክስ መዝገብ ተከሳሽ የነበሩት፤ “ሰርካለም አሣታሚ ድርጅት” 120 ሺህ ብር፣ “ሲሳይ የሕትመትና የማስታወቂያ ድርጅት” 100 ሺህ ብር የተጣለባቸውን ቅጣት እንዲከፍሉ፣ በገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ለቀረበባቸው አፈፃፀም ክስ፣ ጉዳዩ በይቅርታ የተቋጨ በመሆኑ ልንጠየቅ አይገባም ሲሉ መከራከሪያቸውን ለፍርድ ቤት አቀረቡ። ፍርድ ቤቱ መከራከሪያው ለሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ደርሶት ለሰኞ መልስ እንዲሰጥበት አዟል።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
1933 - 2001 ዓ.ም. 




