”ከእስር የተፈታነው በሀገር ሽማግሌዎች ጥረት ነው” ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ

W/t Birtukan MideksaEthiopia Zare (ዓርብ ታህሳስ 3 ቀን 2001 ዓ.ም. December 12, 2008)፦ ምርጫ 97ን ተከትሎ በመንግሥትና በተቃዋሚ ፓርቲዎች መካከል በተፈጠረ አለመግባባት፣ በተነሳ ረብሻ እስር ቤት ገብተው የነበሩት የቀድሞ የቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ተ/ም/ሊቀመንበርና የአሁኑ አንድነት ፓርቲ ፕሬዝዳንት ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ ከእስር የተፈቱበትን ሁኔታ አስመልክቶ፣ ”ይቅርታ አልጠየቅንም የሚል ይዘት ያለው መግለጫ በአውሮፓ ሰጥተዋል” በሚል ጉዳዩን እንዲያብራሩ በፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ወርቅነህ ገበየሁና በአሁኑ ሰዓት ከፍትህ ሚኒስቴር ሚንስትር ዴኤታ ኃላፊነታቸው በተነሱት ዶ/ር ኃሺም መሐመድ ተጠርተው ተጠየቁ። ወ/ት ብርቱካን የሰጡት ምላሽ ለሚመለከተው አካል መተላለፉን መንግሥት አስታውቋል። ሙሉውን አስነብበኝ ...

”የኡጋንዳና የብሩንዲ ወታደሮች እስኪወጡ ከሶማሊያ አንወጣም” ጠ/ሚ መለስ ዜናዊ

PM Meles ZenawiEthiopia Zare (ዓርብ ታህሳስ 3 ቀን 2001 ዓ.ም. December 12, 2008)፦ የኢትዮጵያ ጦር በአስቸኳይ ከሶማሊያ እንዲወጣ ቢወሰንም፤ የሀገሪቱ የመከላከያ ኃይል ጣልቃ በገባበት ወቅት ኢትዮጵያ የወሰደችውን እርምጃ ደግፈው የገቡ የኡጋንዳና የብሩንዲ ወታደሮች እስኪወጡ የኢትዮጵያ ጦር እንደማይወጣ ጠ/ሚ መለስ ዜናዊ አስታወቁ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

ምርጫውን በሚመለከት በቫንኩቨር ውይይት ሊካሄድ ነው

”በወያኔ ምርጫ ማናቸውም ተቀዋሚዎች መሳተፍ የለባቸውም” አቶ አዛለ ደስታ

”ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ምርጫ መገባት አለበት" ተክለሚካኤል አበበ

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ኅዳር 30 ቀን 2001 ዓ.ም. December 9, 2008)፦ በመጪው 2002 ዓ.ም. (2010 እ.ኤ.አ.) ምርጫ በሀገር ቤት የሚገኙ የተቃዋሚ ኃይሎች ምን ማድረግ ይገባቸዋል ከሚል ሃሳብ በመነሳት የመጀመሪያው ህዝባዊ ስብሰባ በቫንኩቨር ካናዳ ቅዳሜ ዲሴምበር 13 ቀን 2008 እ.ኤ.አ. እንደሚካሄድ ተለጸ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

አንድነት ፓርቲ የመጀመሪያ ህዝባዊ ስብሰባ አካሄደ

"ስብሰባው የተሳካ ነበር" ወ/ት ብርቱካን

ዶ/ር ነጋሶ፣ አቶ ስዬ፣ ፕ/ር በየነ፣ ... ተገኝተዋል

UDJ public meeting, Addis Ababa

Ethiopia Zare (ቅዳሜ ኅዳር 27 ቀን 2001 ዓ.ም. December 6, 2008)፦ አብዛኛውን የቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ፓርቲ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ በመያዝ ስያሜውን አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ በማለት ሕጋዊ እውቅና አግኝቶ የሚንቀሳቀሰው አንድነት ፓርቲ ዛሬ የመጀመሪያውን ህዝባዊ ስብሰባ በተሳካ ሁኔታ ተጠናቀቀ። በስብሰባው ላይ የቀድሞው የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ፣ አቶ ስዬ አብርሃ፣ ፕ/ር በየነ ጴጥሮስና ሌሎችም ተገኝተዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ቴዲ አፍሮ የስድስት ዓመት እስራት ተፈረደበት

Teddy Afroዝርዝር ዘገባ የታከለበት

(የፍርድ ውሳኔውን ሙሉ ቃል ይዘናል)

በተጨማሪም የ18 ሺህ ብር ቅጣት ተፈረደበት

“በይግባኝ ወይንም ‘በሽምግልና’ ሊፈታ ይችላል” ታዛቢዎች

Ethiopia Zare (ዓርብ ኅዳር 26 ቀን 2001 ዓ.ም. December 05, 2008)፦ ዝነኛው ድምጻዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ዛሬ በዋለው ችሎት ስድስት ዓመት እስራትና 18 ሺህ ብር ቅጣት ተፈረደበት።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኢትዮጵያ ህዝብ ብዛት 74 ሚሊዮን መድረሱ ይፋ ተደረገ

የአማራ ክልልና አዲስ አበባ ህዝብ ብዛት አከራካሪ ሆኗል

Ethiopia Zare (ዓርብ ኅዳር 26 ቀን 2001 ዓ.ም. December 05, 2008)፦ የኢፌዲሪ የህዝብ ቆጠራ ኮሚሽን የ1999/2000 ዓ.ም. የኢትዮጵያ የህዝብ ቆጠራ የመጀመሪያ ደረጃ ውጤት 73 ሚሊዮን 918 ሺህ 505 መድረሱን አስታወቀ። የአማራ ክልልና አዲስ አበባ ህዝብ ብዛት አከራካሪ ሆኗል። ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኢትዮጵያ ጦር ከሶማሊያ ለቆ መውጣቱን አዘገየ

Ethiopia Zare (ዓርብ ኅዳር 26 ቀን 2001 ዓ.ም. December 05, 2008)፦ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ፣ በሶማሊያ ያለውን የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የሚተካ ጦር እስከሚያዘጋጅ ድረስ፣ ኢትዮጵያ ጦሯን በሶማሊያ ለማቆየት መስማማቷን አንድ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ባለሥልጣን ገለፁ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

ቴዲ አፍሮ ጥፋተኛ ተብሎ ተፈረደበት

ለቅጣት ውሳኔ የፊታችን ዓርብ ተቀጠረ

Teddy Afro

Ethiopia Zare (ሰኞ ኅዳር 22 ቀን 2001 ዓ.ም. December 01, 2008)፦ ለስምንት ወራት ሰው በመኪና ገጭቶ በማምለጥ ወንጀል ተከሶ በእስር ላይ የሚገኘው አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን፣ ዛሬ ኅዳር 22 ቀን በመጥፎነቱ በሚታወቀው የኢትዮጵያ ፍርድ ቤት በዋለው ችሎት ጥፋተኝ ተብሎ እንደተወሰነበት ችሎቱን የተከታተሉ የአዲስ አበባ ምንጮቻችን አስረዱ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...