ባለፉት ሦስት ዓመታት ከግማሽ ሚሊዮን በላይ የአማራ ተወላጆች መፈናቀላቸው ተገለጸ

ዶ/ር ፈንቱ ማንደፍሮ

ከሰሜን ሸዋ፣ ከኦሮሚያ ልዩ ዞን ብቻ ከ300 ሺህ በላይ ተፈናቅለዋል
ችግሩ ባለፉት 30 ዓመታት የተዘራው ጥላቻና ችግሮችን በወቅቱ ማረም ባለመቻሉ መኾኑን ክልሉ አስታወቀ
ተፈናቃዮችን ለመደገፍ ጥሪም ቀርቧል

ኢዛ (ሰኞ ግንቦት ፱ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. May 17, 2021)፦ ባለፉት ሦስት ዓመታት በተዘራው የጥላቻ ትርክትና ጥቃት ከተለያዩ የአገሪቱ ክልሎች ከግማሽ ሚሊዮን በላይ የሚኾኑ የአማራ ክልል ተወላጆች መፈናቀላቸውን የአማራ ክልላዊ መንግሥት አስታውቋል። ከሰሜን ሸዋ እና ከኦሮሚያ ልዩ ዞን አስተዳደር ብቻ ከ300 ሺህ በላይ ዜጐች መፈናቀላቸውም ታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አሳሳቢው የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴ

Ministry of Revenues

በአንድ ሳምንት ከ69 ሚሊዮን ብር ዋጋ ያለው ኮንትሮባንድ ዕቃ በቁጥጥር ሥር ዋለ
41 ተሽከርካሪዎች ኮንትሮባንድ ጭነው ተይዘዋል

ኢዛ (ሰኞ ግንቦት ፱ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. May 17, 2021)፦ በአንድ ሳምንት ውስጥ ከ69 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያላቸው የጦር መሣሪያዎች እና የተለያዩ የኮንትሮባንድ ዕቃዎች መያዙን የገቢዎች ሚኒስቴር አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ከመቶ ቢሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያላቸው ፕሮጀክቶችና ደብዛቸው የጠፋ ኮንትራክተሮች

አይሻ መሐመድ

ሱር ኮንስትራክሽን፣ ተክለብርሃን አምባዬ ኮንስትራክሽን፣ አፍሮ ጽዮን ኮንስትራክሽን በዋቢነት ይጠቀሳሉ

ኢዛ (እሁድ ግንቦት ፰ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. May 16, 2021)፦ ባለፉት ሁለት ዓመታት የግንባታ ሥራዎቻቸው የተስተጓጐለ ትላልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታዎችን፤ ሥራውን ወስደው በነበሩ ኮንትራክተሮች ማስቀጠል ባለመቻሉ በመንግሥት የኮንስትራክሽን ድርጅቶች እንዲሠሩ ስለመወሰኑ ተሰማ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በጸጥታ ኃይሎች በተገደለው ወጣት ላይ ኮምሽኑ የተቃውሞ ድምጹን አሰማ

አማኑኤል ወንድሙ

ገዳዮች ለፍርድ እንዲቀቡም ጠይቋል

ኢዛ (ረቡዕ ግንቦት ፬ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. May 12, 2021)፦ በኦሮሚያ ክልል በድምቢ ዶሎ፣ ቄለም ወለጋ ዞን ትናንት ግንቦት 3 ቀን 2013 ዓ.ም. የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች አንድ በወንጀል ተጠርጣሪን በአደባባይ መግደላቸውን በመጥቀስ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ግድያውን ኮንኗል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በመስቀል አደባባይ የአፍጢር መርኀ ግብር ተካሔደ

አፍጢር በመስቀል አደባባይ

በግብጽ ተይዞ የነበረው የጎዳና ላይ አፍጢር ክብረ ወሰን ዛሬ በኢትዮጵያ ተሰበረ

ኢዛ (ማክሰኞ ግንቦት ፫ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. May 11, 2021)፦ በአዲስ አበባ ከተማ መስቀል አደባባይ የአፍጢር መርኀ ግብር በርካታ ሕዝብ በተገኘበት ተካሔደ። ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር በመርኀ ግብሩ ላይ ተገኝተዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአውሮፓ ሕብረት የምርጫ ታዛቢዎችን እንደሚልክ እርግጥ ኾነ

Ambassador Dina Mufti

አሜሪካ እና ሩሲያም ታዛቢ ይልካሉ

ኢዛ (ማክሰኞ ግንቦት ፫ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. May 11, 2021)፦ የአውሮፓ ሕብረት በኢትዮጵያ የሚካሔደውን ስድስተኛውን አገር አቀፍ ምርጫ 2013 ላለመታዘብ ወስዶ የነበረውን አቋም በመለወጥ፤ ምርጫውን የሚታዘቡ ባለሙያዎች እንደሚልክ ማረጋገጫ መስጠቱን እና የአሜሪካ እና የሩሲያ ታዛቢዎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመጡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በመንግሥት ወጪ የአፍጢር ሥርዓቱ ነገ በመስቀል አደባባይ ይካሔዳል

አዳነች አቤቤ

የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ አዳነች አቤቤ ይቅርታ ጠየቁ

ኢዛ (ሰኞ ግንቦት ፪ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. May 10, 2021)፦ ትናንት በአዲስ አበባ በመስቀል አደባባይ ሊካሔድ የነበረው የረመዳን የአፍጢር ሥነ ሥርዓት ነገ በመስቀል አደባባይ በመንግሥት ወጪ እንዲካሔድ ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአሜሪካ አምባሳደር እና ብፁዕ ወ ቅዱስ አቡነ ማትያስ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ እንደተወያዩ ተገለጸ

ብፁዕ ወ ቅዱስ አቡነ ማትያስ እና ከአምባሳደር ጊታ ፓሲ

ሰሞኑን በቪዲዮ ያስተላለፉት መልእክት እና የትግራይ ሰብአዊ ቀውስ ዋነኛ አጀንዳቸው ነበር

ኢዛ (ሰኞ ግንቦት ፪ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. May 10, 2021)፦ የአሜሪካዋ አምባሳደር ጊታ ፓሲ፤ ብፁዕ ወ ቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓርትሪያክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳስ ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖትን በአምባሳደርዋ መኖሪያ ቤት ተቀብለው ማነጋገራቸው ተሰማ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኦቢኤን ጋዜጠኛ በሸኔ ታጣቂዎች ተገደለ

ሲሳይ ፊዳ

ጋዜጠኛ ሲሳይ ፊዳ የተገደለው በመኖሪያ ቤቱ አቅራቢያ አስፍጠው ሲጠብቁት በነበሩ ሁለት ታጣቂዎች ነው

ኢዛ (ሰኞ ግንቦት ፪ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. May 10, 2021)፦ የኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኔትዎርክ (ኦቢኤን) የምሥራቅ ወለጋ የራዲዮና ቴሌቭዥን ጋዜጠኛ ሲሳይ ፊዳ ትናንት በአካባቢው በሚንቀሳቀሰው ሸማቂ ቡድን መገደሉ ተሰማ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ