የክራር ንግሥቷ አስናቀች ወርቁ በ76 ዓመቷ አረፈች

የክራር ንግስቷ አስናቀች ወርቁየቀብር ሥነ-ሥርዓቷ ነገ በሥላሴ ቤተክርስቲያን ይፈጸማል

Ethiopia Zare (ሐሙስ መስከረም 4 ቀን 2004 ዓ.ም. September 15, 2011)፦ ”የክራሯ ንግሥት” በመባል የምትታወቀው አንጋፋዋ የመድረክ ባለሙያ አስናቀች ወርቁ በ76 ዓመቷ ለረዥም ጊዜ በሕክምና ስትረዳ ከቆየች በኋላ ሕይወቷ አለፈ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

እውቁ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ እስር ቤት ገባ

የመድረክ አመራር አንዷለም አራጌና ሌሎች 3 አባላትም በማዕከላዊ ናቸው

Serkalem Fasi and Eskinder Nega with their sonEthiopia Zare (ረቡዕ መስከረም 3 ቀን 2004 ዓ.ም. September 14, 2011)፦ በደፋርነቱና ለሀገሪቱ መጻኢ ዕድል ያለውን ዕይታ ነጻ የሆኑ ሃሳቦቹን በመግለጽ የሚታወቀው እስክንድር ነጋ እና የአንድነት ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበርና የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አንዷለም አራጌ ወደ ማዕከላዊ እስር ቤት በደህንነቶች ታፍነው መወሰዳቸው ተገለጸ። 

ሙሉውን አስነብበኝ ...

”አዲሱ ዓመት ለኢትዮጵያ በአንድነት የምንሠራበት ዘመን ሊሆን ይገባል” ዳኛ ብርቱካን ሚደቅሳ

ዳኛ ብርቱካን አዲሱን ዓመት በስዊድን ከኢትዮጵያውያን ጋር አሳለፉ

ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ የአዲስ ዓመት የመልካም ምኞት መግለጫ አስተላለፉ

ዳኛ ብርቱካን ሚደቅሳ Judge Birtukan Mideksa

Ethiopia Zare (ሰኞ መስከረም 1 ቀን 2004 ዓ.ም. September 12, 2011)፦ ዳኛ ብርቱካን ሚደቅሳ በስዊድን ዋና ከተማ ስቶክሆልም ከኢትዮጵያውያን ጋር አዲሱን ዓመት ለመቀበል በተዘጋጀ ልዩ ዝግጅት ላይ በመገኘት በስደት ላይ ለሚገኙና በሀገር ውስጥ ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የአዲስ ዓመት የመልካም ምኞታቸውን ገለጹ። ዜጎችን ያስጎነበሰውን የየሀገራቸውን ሥርዓት ለሁልጊዜ እንደቀየሩት ህዝቦች ሁሉ፤ በአዲስ ተስፋ፣ በአዲስ ሃሳብ ለኢትዮጵያ በአንድነት የምንሠራበት ዘመን ሊሆን ይገባል ሲሉ ተናገሩ። 

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በዚህ ዓመት የጀግኖች ምሽት ዝግጅት እንደማይኖር ተነገረ

የኢትዮጵያዊነት ውርስና ቅርስ ድርጅት አዲስ አመራር ኮሚቴ መረጠ

Ethiopia Zare (አርብ መስከረም 1 ቀን 2004 ዓ.ም. September 12, 2011)፦ ላለፉት ሶስት አመታት በየአመቱ በተከታታይ ሲካሄድ የቆየው፡ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የኢትዮጵያን ሉአላዊነት በመከላከልና በማስጠበቅ ሲተጉ የኖሩ የጦር መኮንኖችንና ታጋዮች የሚሸልሙበት የጀግኖች ምሽት ዝግጅት እንደማይኖር አንዳንድ ውስጣዊ ምንጮች ገለጹ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

አርቲስት ደበበ እሸቱ በሽብርተኛነት ክስ ማእከላዊ ታሰረ

በሽብርተኛ ክስ ውብሸት ጥላሁን፣ ርዮት አለሙ እና ሁለት የስዊድን ጋዜጠኞች ክስ ተመስርቶባቸዋል

Ethiopia Zare (አርብ ጳጉሜን 4 ቀን 2003 ዓ.ም. September 9, 2011)፦ ታዋቂው የጥበብ ባለሙያና የቅንጅት ለአንድነትና ዲሞክራሲ አመራር አባል እንደነበር የሚታወቀው አርቲስት ደበበ እሸቱ በኢህአዴግ መንግስት “ሽብርተኛ” ተብሎ ከተፈረጀው ግንቦት 7 ንቅናቄ ጋር ግንኙነት አድርጓል በሚል ማእከላዊ እስር ቤት መግባቱ ተገለጸ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

የጋዳፊ ቤተሰቦች ፊቷን ያቃጠሏት ኢትዮጵያዊት የሕክምና ዕርዳታ እያገኘች ነው

[ማሳሰቢያ፦ ቪዲዮውን ሕፃናት አይዩት!]

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ነኀሴ 24 ቀን 2003 ዓ.ም. August 30, 2011)፦ የሊቢያው መሪ ልጅ የሆነው የሃኒባል ጋዳፊ ባለቤት ወ/ሮ ኤሊን በፈላ ውሃ ከአናትዋ ጀምሮ ፊትዋንና መላ ሰውነቷን ያቃጠለቻት የ30 ዓመቷን ኢትዮጵያዊት ወጣት ሸዋዬ ሞላ በትሪፖሊ ሆስፒታል እርዳታ እየተደረገላት መሆኑን ሲኤንኤን ዘገበ። አደጋውን ያደረሱት አልጄሪያ ተሰድደዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የጋዳፊ ልጅ ሚስት ኢትዮጵያዊቷን በፈላ ውሃ ለበለበቻት

[ማሳሰቢያ፦ ለሕፃናት ያልተፈቀደ!]

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ነኀሴ 24 ቀን 2003 ዓ.ም. August 30, 2011)፦ የሊቢያው መሪ ሙአመር ጋዳፊ ልጅ የሆነው ሃኒባል ጋዳፊ ባለቤት ወ/ሮ ኤሊን የ30 ወጣት ሸዋዬ ሞላ የተባለች ኢትዮጵያዊቷን የልጆችዋን ሞግዚት የፈላ ውሃ ከአናቷ ጀምራ መላ አከላቷ ላይ ደጋግማ በማፍሰስ እንዳቃጠለቻት ሲኤንኤን የተሰኘው ቴሌቭዥን አጋለጠ። የሙአመር ጋዳፊ ቤተሰቦች እንዲህ በመሰው ጭካኔና ግፍ በተሞላበት መንገድ ሰዎችን ላለፉት 42 ዓመታት ሲያሰቃዩ፣ ሲጨፈጭፉ፣ ሲገርፉ፣ ሲገድሉ፣ ... እንደነበር ይታወቃል። ሙሉውን የሲኤንኤን ዘገባ የማጫወቻ ቁልፉን በመጫን ይመልከቱ! [ዘገባውን ሕፃናት ሊያዩት አይገባም!]

አድባር፡ ሶስተኛውን ክርክር በቶሮንቶ አዘጋጅቷል

           ዲሜጥሮስ ብርቁና ተክሌ አበበ መርጋ ይከራከራሉ

Ethiopia Zare (አርብ ነሐሴ 20 ቀን 2003 ዓ.ም August 26 2011) :- ባለፈው ግንቦት የተቋቋመውና መቀመጫው በቶሮንቶ የሆነው “አድባር የክርክር ማህበር” ሶስተኛውን የክርክር ዝግጅት በያዝነው ሳምንት፡ አርብ፡ ኦገስት 26 ከሰዓት በኋላ፡ ከ5 ሰዓት ጀምሮ፡ በሂሩት የሀበሻ ሬስቶራንት እንደሚያደርግ በላከው አጭር መግለጫ አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ዲባቶ አረጋዊ በርሄ ከኦታዋ ኢትዮጵያዊያን ጋር መከረ

ስብሰባው በካሜራ እንዲቀረጽ ተፈቅዷል

ለተቃዋሚ ሀይሎች ኅብረት ምስረታ ከግንቦት ሰባትና ሌሎች ተቃዋሚ ሀይሎች ጋር እየሰራን ነው” 

Ethiopia Zare (ሰኞ ነሐሴ 14 ቀን 2003 ዓ.ም August 14 2011) ቀውሱ ያለው አሮጌው ስርአት እየወደቀ፡ አዲሱ ስርአት ግን አልወለድ ማለቱ ላይ ነውበሚለው የኢጣሊያዊው ፈላስፋና ፖለቲከኛ የሁለተኛ ዓለም ጦርነት ዋዜማ ንግግር ጥቅስ መልእክቱን አጽንኦት የሰጠው፡ የኢትዮጵያን የህዝብ ፍሰትና ፍልሰት ታሪክ አንስቶ፡ በዘመናዊ ታሪኳ ኢትዮጵያ የገባችበትን ቀውስ ጠቅሶ፡ በዋንኛነት አሁን ኢትዮጵያ ያጋጠማትን አደጋ ያብራራው የቀድሞ የህወሀት መስራች፡ የታንድ (የትግራይ ትብብር ለብሄራዊ ዴሞክራሲ) መሪ ዲባቶ አረጋዊ በርሄ፡ በኦታዋ ከሚገኙ አያሌ አገር ወዳድ ኢትዮጵያዊአን ጋር ገንቢ ውይይት አድርጓል።
ሙሉውን አስነብበኝ ...

ዲባቶ አረጋዊ በርሄ ኦታዋን ያነጋግራሉ! ወ/ሮ አረጋሽ አዳነ ሕዝቡን አመሰገኑ

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ነሐሴ 8 ቀን 2003 ዓ.ምAugust 16)  የቀድሞ የሕወሀት መስራችና የነጻነት ታጋዩ ዲባቶ አረጋዊ በርሄ በመጪው ቅዳሜ፡ ኦገስት 20 በካናዳ ዋና ከተማ፡ ኦታዋ ህዝባዊ ስብሰባ እንደሚያደርጉ ከኦታዋ የሚተላለፈው የኢትዮጵያ ሬድዮ ዘገበ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...