የብጹዕ ሊቀ ጳጳስ አቡነ ዜና ማርቆስ የቀብር ስነ ስርአት በሲያትል ይፈጸማል
Ethiopia Zare (ረቡዕ ሐምሌ 26 ቀን 2003 ዓ.ም August 3, 2011):- በብጹዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሪዎስ ፓትሪያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ የሚመራው ሕጋዊው ቅዱስ ሲኖዶስ የብጹእ ሊቀ ጳጳስ አቡነ ዜና ማርቆስ ክቡር ሥጋ የሚያርፍበት ቦታ ለማዘጋጀት ባወጣው እቅድ መሰረት በስማቸው በተሰየመውና ቴክሳስ - ሂውስተን በተመሰረተው ገዳም ለማሳረፍ ያደረጋቸው ሙከራዎች ጊዜ በመውሰዱ ለጊዜው ብጹእነታቸው ብርታት ከእዳ ነጻ አድርገው በሲያትል ከተማ ባቋቋሙት መካነ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ካቴድራል የቀብር ስነስርአታቸው እንዲፈጸም ወሰነ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...


