የአውራምባ ታይምስ ም/ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ ታሰረ

”ጉዳዩ ከጋዜጣዋ ጋርም ሆነ ከሙያው ጋር ተያያዥነት የለውም” የመንግሥት የፀጥታ ተቋማት

”ጋዜጠኛው ለእስር የተዳረገበትን ምክንያትና የሚገኝበትን ሁኔታ መንግሥት ያሳውቀንአውራምባ ታይምስ

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ሰኔ 14 ቀን 2003 ዓ.ም. June 21, 2011)፦ የአውራምባ ታይምስ ም/ዋና አዘጋጅ የሆነው ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ እሁድ ሰኔ 12 ቀን 2003 ዓ.ም ከቀኑ 9፡00 ሰዓት አካባቢ በርካታ ቁጥር ባላቸው የፀጥታ ኃይሎች ተይዞ ከመኖሪያ ቤቱ መታሰሩን አውራምባ ታይምስ ከቤተሰቦቹ ማረጋገጡን ባወጣው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በሕወሐት ወዳጅነት የሚታወቀው የሲ.አይ.ኤ ከፍተኛ ሰላይ በሞት ተለየ

  • አሜሪካዊው ሰላይ በለንደኑ ጉባኤ ቁልፍ ሰው ነበር
  • የደርግ ደህንነት ሹም ኮ/ል ተስፋዬ ቀብር ተፈጸመ

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ሰኔ 7 ቀን 2003 ዓ.ም. June 13, 2011)፦ የሕወሀት ጥብቅ ወዳጅና ከደርግ መንግስት ውድቀት በፊት የለንደኑ ጉባኤ አቀናባሪ ፖል ሄንዝ ህይወት ማለፉ ተሰማ። የደርግ የደህንነት ሹም ኮ/ል ተስፋዬ ወ/ስላሴ ቀብር ስነስርአት ተፈጸመ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

በኤርትራ የእሳተ ገሞራ ፈነዳ

ሂላሪ ክሊንተን የአዲስ አበባ ጉብኝታቸውን አቋረጡ

Ethiopia Zare (ሰኞ ሰኔ 6 ቀን 2003 ዓ.ም. June 13, 2011)፦ ትላንት እሁድ ምሽት ላይ በቀይ ባህር በስተደቡብ ክልል በተከሰተ የእሳተ ገሞራ ፍንዳታ ምክንያት በአዲስ አበባ የነበሩት የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስተር ሂላሪ ክሊንተን በአፋጣኝ ሀገር መልቀቃቸው ተዘገበ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

አባይን ለመገደብ በሚል በመላ ሀገሪቱ የሚሰበሰብ ገንዘብ መጠን አልተገለጸም

ለሸቀጦች ዋጋ ከፍ ዝቅ ማለት ምክንያት ሆኗል ተባለ

Ethiopia Zare (ሰኞ ሰኔ 6 ቀን 2003 ዓ.ም. June 13, 2011)፦ አባይን ለመገደብ ከህዝብ የሚሰበሰበውንና ከቦንድ ሽያጭ የሚገኘውን ገንዘብ መንግስት ወደ ካዝና ማስገባቱ ለዋጋ ግሽበቱ ጠንቅ ሊሆን እንደሚችል የኢኮኖሚ ተንታኞች ስጋታቸውን ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የዶ/ር ታዬ ወልደሰማያት ባለቤት ወ/ሮ አስቴር አረፉ

Ethiopia Zare (ሰኞ ሰኔ 6 ቀን 2003 ዓ.ም. June 13, 2011)፦ የአንጋፋው የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር መሪ የነበሩት የፖለቲካ ሳይንቲስት ዶ/ር ታዬ ወልደሰማያት ባለቤት ከዚህ አለም በሞት መለየታቸውንና የቀብር ስነ ስርአታቸውም በእስጢፋኖስ ቤተ ክርስቲያን መፈጸሙን የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች ከአዲስ አበባ ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ከኖርዌይ ወደ ስዊድን ገቡ

በአዶልፍ ፍሬድሪክ ቤተክርስቲያን ተጠልለዋል

Ethiopia Zare (ቅዳሜ ሰኔ 4 ቀን 2003 ዓ.ም. June 11, 2011)፦ ለረጅም ዓመታት በኖርዌይ ይኖሩ የነበሩ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች የደረሰባቸውን በደል ለሌሎች መንግሥታት ለማሳወቅና ተቀባይ ሀገር ለመፈለግ ወደ ስዊድን ገብተው በአዶልፍ ፍሬድሪክ ቤተክርስቲያን መጠለላችውን የስደተኖቹ ተወካይ አቶ ልዑል ታደሰ ለኢትዮጵያ ዛሬ ገለጹ። 

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አንድ ሄክታር መሬት ከሃያ ብር ባነሰ

በኢትዮጵያ እየተካሄደ ስላለው የመሬት ነጠቃ የተዘጋጀ ልዩ ጥናታዊ ዘገባ

መንግሥት ከቀያቸው ያፈናቀላቸው ነዋሪዎች Government displace people

Ethiopia Zare (ዓርብ ሰኔ 3 ቀን 2003 ዓ.ም. June 10, 2011)፦ አንድ ሄክታር መሬት በአንድ ዶላር ከ19 ሣንቲም (በኢትዮጵያ ከሃያ ብር ባነሰ ገንዘብ) በ”ኢንቨስትመንት” ስም ለ99 ዓመታት በሚቆይ ሊዝ የኢህአዴግ መንግሥት የኢትዮጵያን መሬት እየቸበቸበ፤ ህዝቡን ለዘመናት ከኖረበት ቀዬ እያፈናቀለ መሆኑን የኦክላንድ ተቋም እና የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ በቅንጅት ባካሄዱት የጥናት ዘገባ ገለፁ። 

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በኦጋዴን አካባቢ ውጥረቱ ተባብሷል

'የአለም ምግብ ድርጅት ታጋቾችን ነጻ አውጥቻለሁ' ኦብነግ

Ethiopia Zare (ሐሙስ ግንቦት 25 ቀን 2003 ዓ.ም. June 2, 2011)፦ በኦጋዴን ክልል የትጥቅ ትግል የሚያካሂደው የኦጋዴን ብሄራዊ ነጻነት ግንባር በቅርቡ ባደረገው ከፍተኛ የጥቃት እርምጃ ጂጂጋ አካባቢ የሚገኘውን የጋላሽ ከተማን ተቆጣጥሮ በመቶዎች የሚቆጠሩ እስረኞችን ነጻ ማውጣቱንና ብዛት ያላቸው የጦር መሳሪያዎችን መማረኩን ገልጿል። 

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የደርግ ባለስልጣናት የሞት ፍርድ ወደ እድሜ ልክ ተቀየረ

የ23ቱን ስም ዝርዝር ይዘናል

Ethiopiaz Zare (ረቡዕ ግንቦት 24 ቀን 2003 ዓ.ም. June 1, 2011)፦ በመጥፎነቱ የሚታወቀው በቀድሞው የኢትዮጵያ መንግስት አመራሮች በእነ ኮሎኔል መንግስቱ ኃይለምሪያም ክስ መዝገብ ስር በዘር ማጥፋት ወንጀል ተከሰው የሞት ፍርድ የተወሰነባቸው የደርግ ባለስልጣናት የቅጣት ውሳኔ ወደ እድሜ ልክ መለወጡ ተገለጸ። 

ሙሉውን አስነብበኝ ...