“የፖለቲካ አስረኞቹ በአስቸኳይ ይፈቱ!” በሰሜን አሜሪካ የመኢአድ ድጋፍ ሰጭ ማኅበር

AEUP support in North AmericaEthiopia Zare (ዓርብ መስከረም 12 ቀን 2004 ዓ.ም. September 23, 2011)፦ ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ “ከሽብርተኞች ጋር ንክኪ አላቸው” የሚል መሰረተ ቢስ ክስ እየመሰረተ በርካታ የተቃዋሚ ፓርቲዎች አመራር አባላትን፣ የነፃው ፕሬስ ጋዜጠኞችንና አርቲስቶችን ወደ እስር ማጎሩን አስመልክቶ በሰሜን አሜሪካ የመኢአድ ድጋፍ ሰጪ ማኅበር ትናንት ባወጣው መግለጫ እስረኞቹ ባስቸኳይ እንዲፈቱ ጠይቋል። ሙሉውን አስነብበኝ ...

”የታሰሩት ፖለቲከኞችና ጋዜጠኞች አባላቶቼ አይሉም” ግንቦት 7

Ethiopia Zare (ሐሙስ መስከረም 11 ቀን 2004 ዓ.ም. September 22, 2011)፦ ባለፈው መስከረም 3 ቀን 2004 ዓ.ም. የአንድነት ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር አንዷለም አራጌንና ሌሎች ሦስት የፓርቲውን የምክር ቤት አባላትና እውቁን ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋን ጨምሮ ከግንቦት ሰባት ጋር ግንኙነት አላቸው በማለት ኢህአዴግ ያሠራቸው ግለሰቦች ”ከእኔ ጋር ምንም ግንኙነት የላቸውም” በማለት ግንቦት ሰባት መግለጫ አወጣ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኢሕአዴግ መንግስት 52 ቢሊየን ባለ100 እና 50 ብር ኖቶች ሊያሳትም ነው

ግሽበቱን ያባብሰዋለረ ተብሎ ተሰግቷል

Ethiopia Zare (ቅዳሜ መስከረም 6 ቀን 2004 ዓ.ም. September 17, 2011)፦ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ 52 ቢሊዮን ብር ዋጋ ያላቸው አዳዲስ የመቶ እና የሃምሣ ብር ኖቶችን ሊያሳትም መዘጋጀቱ ተሰማ። በሀገሪቱ ታሪክ ይህንን ያህል መጠን ያለው ገንዘብ ታትሞ የማያውቅ ሲሆን ለማሳተም ብቻ ከግማሽ ቢሊየን ብር በላይ እንደሚፈጅ ተገምቷል። ሙሉውን አስነብበኝ ...

የክራር ንግሥቷ አስናቀች ወርቁ በ76 ዓመቷ አረፈች

የክራር ንግስቷ አስናቀች ወርቁየቀብር ሥነ-ሥርዓቷ ነገ በሥላሴ ቤተክርስቲያን ይፈጸማል

Ethiopia Zare (ሐሙስ መስከረም 4 ቀን 2004 ዓ.ም. September 15, 2011)፦ ”የክራሯ ንግሥት” በመባል የምትታወቀው አንጋፋዋ የመድረክ ባለሙያ አስናቀች ወርቁ በ76 ዓመቷ ለረዥም ጊዜ በሕክምና ስትረዳ ከቆየች በኋላ ሕይወቷ አለፈ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

እውቁ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ እስር ቤት ገባ

የመድረክ አመራር አንዷለም አራጌና ሌሎች 3 አባላትም በማዕከላዊ ናቸው

Serkalem Fasi and Eskinder Nega with their sonEthiopia Zare (ረቡዕ መስከረም 3 ቀን 2004 ዓ.ም. September 14, 2011)፦ በደፋርነቱና ለሀገሪቱ መጻኢ ዕድል ያለውን ዕይታ ነጻ የሆኑ ሃሳቦቹን በመግለጽ የሚታወቀው እስክንድር ነጋ እና የአንድነት ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበርና የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አንዷለም አራጌ ወደ ማዕከላዊ እስር ቤት በደህንነቶች ታፍነው መወሰዳቸው ተገለጸ። 

ሙሉውን አስነብበኝ ...

”አዲሱ ዓመት ለኢትዮጵያ በአንድነት የምንሠራበት ዘመን ሊሆን ይገባል” ዳኛ ብርቱካን ሚደቅሳ

ዳኛ ብርቱካን አዲሱን ዓመት በስዊድን ከኢትዮጵያውያን ጋር አሳለፉ

ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ የአዲስ ዓመት የመልካም ምኞት መግለጫ አስተላለፉ

ዳኛ ብርቱካን ሚደቅሳ Judge Birtukan Mideksa

Ethiopia Zare (ሰኞ መስከረም 1 ቀን 2004 ዓ.ም. September 12, 2011)፦ ዳኛ ብርቱካን ሚደቅሳ በስዊድን ዋና ከተማ ስቶክሆልም ከኢትዮጵያውያን ጋር አዲሱን ዓመት ለመቀበል በተዘጋጀ ልዩ ዝግጅት ላይ በመገኘት በስደት ላይ ለሚገኙና በሀገር ውስጥ ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የአዲስ ዓመት የመልካም ምኞታቸውን ገለጹ። ዜጎችን ያስጎነበሰውን የየሀገራቸውን ሥርዓት ለሁልጊዜ እንደቀየሩት ህዝቦች ሁሉ፤ በአዲስ ተስፋ፣ በአዲስ ሃሳብ ለኢትዮጵያ በአንድነት የምንሠራበት ዘመን ሊሆን ይገባል ሲሉ ተናገሩ። 

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በዚህ ዓመት የጀግኖች ምሽት ዝግጅት እንደማይኖር ተነገረ

የኢትዮጵያዊነት ውርስና ቅርስ ድርጅት አዲስ አመራር ኮሚቴ መረጠ

Ethiopia Zare (አርብ መስከረም 1 ቀን 2004 ዓ.ም. September 12, 2011)፦ ላለፉት ሶስት አመታት በየአመቱ በተከታታይ ሲካሄድ የቆየው፡ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የኢትዮጵያን ሉአላዊነት በመከላከልና በማስጠበቅ ሲተጉ የኖሩ የጦር መኮንኖችንና ታጋዮች የሚሸልሙበት የጀግኖች ምሽት ዝግጅት እንደማይኖር አንዳንድ ውስጣዊ ምንጮች ገለጹ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

አርቲስት ደበበ እሸቱ በሽብርተኛነት ክስ ማእከላዊ ታሰረ

በሽብርተኛ ክስ ውብሸት ጥላሁን፣ ርዮት አለሙ እና ሁለት የስዊድን ጋዜጠኞች ክስ ተመስርቶባቸዋል

Ethiopia Zare (አርብ ጳጉሜን 4 ቀን 2003 ዓ.ም. September 9, 2011)፦ ታዋቂው የጥበብ ባለሙያና የቅንጅት ለአንድነትና ዲሞክራሲ አመራር አባል እንደነበር የሚታወቀው አርቲስት ደበበ እሸቱ በኢህአዴግ መንግስት “ሽብርተኛ” ተብሎ ከተፈረጀው ግንቦት 7 ንቅናቄ ጋር ግንኙነት አድርጓል በሚል ማእከላዊ እስር ቤት መግባቱ ተገለጸ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

የጋዳፊ ቤተሰቦች ፊቷን ያቃጠሏት ኢትዮጵያዊት የሕክምና ዕርዳታ እያገኘች ነው

[ማሳሰቢያ፦ ቪዲዮውን ሕፃናት አይዩት!]

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ነኀሴ 24 ቀን 2003 ዓ.ም. August 30, 2011)፦ የሊቢያው መሪ ልጅ የሆነው የሃኒባል ጋዳፊ ባለቤት ወ/ሮ ኤሊን በፈላ ውሃ ከአናትዋ ጀምሮ ፊትዋንና መላ ሰውነቷን ያቃጠለቻት የ30 ዓመቷን ኢትዮጵያዊት ወጣት ሸዋዬ ሞላ በትሪፖሊ ሆስፒታል እርዳታ እየተደረገላት መሆኑን ሲኤንኤን ዘገበ። አደጋውን ያደረሱት አልጄሪያ ተሰድደዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የጋዳፊ ልጅ ሚስት ኢትዮጵያዊቷን በፈላ ውሃ ለበለበቻት

[ማሳሰቢያ፦ ለሕፃናት ያልተፈቀደ!]

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ነኀሴ 24 ቀን 2003 ዓ.ም. August 30, 2011)፦ የሊቢያው መሪ ሙአመር ጋዳፊ ልጅ የሆነው ሃኒባል ጋዳፊ ባለቤት ወ/ሮ ኤሊን የ30 ወጣት ሸዋዬ ሞላ የተባለች ኢትዮጵያዊቷን የልጆችዋን ሞግዚት የፈላ ውሃ ከአናቷ ጀምራ መላ አከላቷ ላይ ደጋግማ በማፍሰስ እንዳቃጠለቻት ሲኤንኤን የተሰኘው ቴሌቭዥን አጋለጠ። የሙአመር ጋዳፊ ቤተሰቦች እንዲህ በመሰው ጭካኔና ግፍ በተሞላበት መንገድ ሰዎችን ላለፉት 42 ዓመታት ሲያሰቃዩ፣ ሲጨፈጭፉ፣ ሲገርፉ፣ ሲገድሉ፣ ... እንደነበር ይታወቃል። ሙሉውን የሲኤንኤን ዘገባ የማጫወቻ ቁልፉን በመጫን ይመልከቱ! [ዘገባውን ሕፃናት ሊያዩት አይገባም!]