አድባር፡ ሶስተኛውን ክርክር በቶሮንቶ አዘጋጅቷል

           ዲሜጥሮስ ብርቁና ተክሌ አበበ መርጋ ይከራከራሉ

Ethiopia Zare (አርብ ነሐሴ 20 ቀን 2003 ዓ.ም August 26 2011) :- ባለፈው ግንቦት የተቋቋመውና መቀመጫው በቶሮንቶ የሆነው “አድባር የክርክር ማህበር” ሶስተኛውን የክርክር ዝግጅት በያዝነው ሳምንት፡ አርብ፡ ኦገስት 26 ከሰዓት በኋላ፡ ከ5 ሰዓት ጀምሮ፡ በሂሩት የሀበሻ ሬስቶራንት እንደሚያደርግ በላከው አጭር መግለጫ አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ዲባቶ አረጋዊ በርሄ ከኦታዋ ኢትዮጵያዊያን ጋር መከረ

ስብሰባው በካሜራ እንዲቀረጽ ተፈቅዷል

ለተቃዋሚ ሀይሎች ኅብረት ምስረታ ከግንቦት ሰባትና ሌሎች ተቃዋሚ ሀይሎች ጋር እየሰራን ነው” 

Ethiopia Zare (ሰኞ ነሐሴ 14 ቀን 2003 ዓ.ም August 14 2011) ቀውሱ ያለው አሮጌው ስርአት እየወደቀ፡ አዲሱ ስርአት ግን አልወለድ ማለቱ ላይ ነውበሚለው የኢጣሊያዊው ፈላስፋና ፖለቲከኛ የሁለተኛ ዓለም ጦርነት ዋዜማ ንግግር ጥቅስ መልእክቱን አጽንኦት የሰጠው፡ የኢትዮጵያን የህዝብ ፍሰትና ፍልሰት ታሪክ አንስቶ፡ በዘመናዊ ታሪኳ ኢትዮጵያ የገባችበትን ቀውስ ጠቅሶ፡ በዋንኛነት አሁን ኢትዮጵያ ያጋጠማትን አደጋ ያብራራው የቀድሞ የህወሀት መስራች፡ የታንድ (የትግራይ ትብብር ለብሄራዊ ዴሞክራሲ) መሪ ዲባቶ አረጋዊ በርሄ፡ በኦታዋ ከሚገኙ አያሌ አገር ወዳድ ኢትዮጵያዊአን ጋር ገንቢ ውይይት አድርጓል።
ሙሉውን አስነብበኝ ...

ዲባቶ አረጋዊ በርሄ ኦታዋን ያነጋግራሉ! ወ/ሮ አረጋሽ አዳነ ሕዝቡን አመሰገኑ

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ነሐሴ 8 ቀን 2003 ዓ.ምAugust 16)  የቀድሞ የሕወሀት መስራችና የነጻነት ታጋዩ ዲባቶ አረጋዊ በርሄ በመጪው ቅዳሜ፡ ኦገስት 20 በካናዳ ዋና ከተማ፡ ኦታዋ ህዝባዊ ስብሰባ እንደሚያደርጉ ከኦታዋ የሚተላለፈው የኢትዮጵያ ሬድዮ ዘገበ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የብጹዕ ሊቀ ጳጳስ አቡነ ዜና ማርቆስ የቀብር ስነ ስርአት በሲያትል ይፈጸማል

Ethiopia Zare (ረቡዕ ሐምሌ 26 ቀን 2003 ዓ.ም August 3, 2011):- በብጹዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሪዎስ ፓትሪያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ የሚመራው ሕጋዊው ቅዱስ ሲኖዶስ የብጹእ ሊቀ ጳጳስ አቡነ ዜና ማርቆስ ክቡር ሥጋ የሚያርፍበት ቦታ ለማዘጋጀት ባወጣው እቅድ መሰረት በስማቸው በተሰየመውና ቴክሳስ - ሂውስተን በተመሰረተው ገዳም ለማሳረፍ ያደረጋቸው ሙከራዎች ጊዜ በመውሰዱ ለጊዜው ብጹእነታቸው ብርታት ከእዳ ነጻ አድርገው በሲያትል ከተማ ባቋቋሙት መካነ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ካቴድራል የቀብር ስነስርአታቸው እንዲፈጸም ወሰነ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኦታዋው ግልጽ ህዝባዊ ስብሰባ፡ በስውር ተጠናቀቀ

የብሄር ድርጅቶችን፡ አቅርቦ መያዝ እንጂ፡ ሙሉ በሙሉ ማግለሉ አግባብ አይደለም እኔ

የብሄር ድርጅቶችን እንደውም መድረክ በመስጠት ማጠናከር ሳይሆን ማጥፋት ነው አንድ ተሳታፊ 

የኢትዮጵያን አንድነት የማይቀበሉ የብሄር ድርጅቶችን እንደውም ወደፊት እንደወያኔ የምንዋጋቸው ናቸው ዶ/ር ኤርሚያስ ዓለሙ 


ልዩ ዘገባ - ልጅ ተክሌ (ኦታዋ-ካናዳ)

 

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ሐምሌ 19 ቀን 2003 ዓ.ም. July 14, 2011):- እሁድ ጁላይ 24፡ 2011 ዓ.ም.፡ መቀመጫው በኦታዋ የሆነው፡ “የኢትዮጵያ ካናዳዊያን መድረክ ለዴሞክራሲ” (በእንግሊዘኛው “Ethio-Canadians Forum for Democracy”፡ ከፖለቲካ እስረኞች አንድነት ማህበር፡ ከኢህአፓና፡ ከዓለም-አቀፋዊው የፖለቲካ ድርጅቶች ትብብር ምስረታ አዘጋጅ ኮሚቴ ጋር በመተባበር፡ በኦታዋ ያዘጋጀው ስብሰባ የተለያዩ፡ ሀሳቦች ተንሸራሽረውበት ተጠናቀቀ። ዝግጅቱ ግን እንዳይቀረጽ መከልከሉ ጥቂቶችን አስቆጥቷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የምስራቅ ኢትዮጵያ አስከፊ ረሃብ አሳሳቢ ሆኗል

ሊያነቡት የሚገባ ልዩ ዘገባ - ከአዲስ አበባ ዘጋቢያችን

Ethiopia Zare (ሐሙስ ሐምሌ 7 ቀን 2003 ዓ.ም. July 14, 2011):- ህጻናት ረሃብ ሳል እአሰሙ ነው። እናቶች የልጆቻቸውን አሰቃቂ ሞት በአይናቸው ለማየት ተገደዋል። እርፍ ጨብጠው መሬቱን እገመሰ ዘርቶ፣ አችዶና ሰብስቦ ለሌላው ይተርፍ የነበረው ገበሬ ተስፋ የቆረጡ አይኖቹ እንባቸው ደርቋል። ለሰው ልጆች ተስፋ የነበሩት ዕጸዋት ጠውልገዋል።ከብቶች በሜዳው ላይ ወድቀዋል። የተስፋ ጭላንጭል ተዳፍኖ የሞት ደመና በሚሊየኖች የሚቆሩ ኢትዮጵያዊያን ላይ አንዣቧ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...

በመጨረሻም ብርቱካንም ተናገረች፤ ያምቡሌም ተዘፈነ፡ ወጣቶቹም ሮጡ፡ ኢትዮጵያም ተከበረች፡ ፌስቲቫላችንም ተሳካ፡

(የግል ዘገባ - በልጅ ተክሌ)

ብዙዎች አስቦክተውን፡ ብዙዎችም አስጠንቅቀውን ነበር

 አንዳንዶቹ፡ “አይ አይሳካላችሁም፡ እንደው ነው የምትደክሙት” ብለው አስፈራርተውን ነበር። ገሚሶቹም፡ “ባዶ ሜዳ ታቅፋችሁ ትቀራላችሁ” ብለው ፈልፍለውብን ነበር። የተቀሩት ግን “በርቱ፡ እኛም እንመጣለን” አሉን። እነሆ ገሚሱን ታቅፈን፡ ገሚሱንም አዝለን ወደፊት ገሰገስን፤ የዛሬ አስር ወር በሀሳብ ደረጃ፡ የዛሬ ስድስት ወር በህግ ደረጃ፡ የዛሬ ሁለት ወር ወዲህ ደግሞ በተጨባች የተያዘውን ፌስቲቫል አርብ ስንከፍት ግን፡ ገና ከመክፈቻው ሰዓት አስቀድሞ የመክፈቻው አዳራሽ ላይ የተጠራቀሙት ሰዎች ቁጥር ተስፋ ፈንጣቂ ነበር።

 

ሙሉውን አስነብበኝ ...

“ዛሬም ስለ ሀገሬ ተስፋ አደርጋለሁ፤ አጠንክሬ ህልም አልማለሁ” ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ

          ‘ኢትዮጵያ የነጻነት ሀገር አይደለችም፤ የፍትህ አገር አይደለችም’

Ethiopia Zare ማክሰኞ ሰኔ 28 ቀን 2003 ዓ.ም. July 5, 2011:- ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ የኢትዮጵያዊያን ውርስና ቅርስ ማህበር በዋሽንግተን ዲሲ ባዘጋጀው ፌስቲቫል በህዝብ ፊት ለመጀመሪያ ጊዜ ንግግር አደረገች። የቪድዮ መልእክታ ተሰራጭቷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኢትዮጵያዊነት ውርስና ቅርስ ሁለተኛ ቀን ባስደሳች ሁኔታ አለፈ

Ethiopia Zare (እሁድ ሰኔ 26 ቀን 2011 .. July 3 , 2011):- አርብ፡ ጁላይ 1 ቀን በዋሽንግተን ከተማ በመቶዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን በተገኙበት በደማቅ ሁኔታ የተከፈተው የኢትዮጵያዊነት ውርስና ቅርስ ማህበረሰብ በሰሜን አሜሪካ ያዘጋጀው የመጀመሪያው የኢትዮጵያ አመታዊ ፌስቲቫል  በሁለተኛው ቀን በተሳካ ሁኔታ ቀጥሎ ውሏል። ዛሬ እሁድ ፍጻሜ ይሆናል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ