ከ97 ምርጫ በኋላ የት እንደደረሱ ያልታወቁ ዜጎች መኖራቸውን ኢሰመጉ ገለጸ

Ethiopia Zare (ሐሙስ ኅዳር 30 ቀን 2003 ዓ.ም. December 9, 2010)፦ በኢትዮጵያ ብቸኛው የሰብአዊ መብት ተሟጋች የሆነው የሰብአዊ መብቶች ጉባኤ ከረጀረም ጊዜ ቆይታ በኋላ የመብቶች ጥሰትን የሚያሳየውን 34ኛ መግለጫ ይፋ አደረገ። ከምርጫ 97 ጋር በተያያዘ የደረሱበት ያልታወቁ ዜጎች መኖራቸውን አትቷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በስዊድን ’’እውነትም እኛ …” ተመረቀ

ግምገማና ውይይት ተደረገ

Sweden, Stockholm 27th November 2010

Ethiopia Zare (ሰኞ ኅዳር 27 ቀን 2003 ዓ.ም. December 6, 2010)፦ በጋዜጠኛና ደራሲ አበራ ለማ ተገጥሞ በራሳቸው አንባቢነትና በአቶ ክብረት መኮንን የምስልና ድምፅ ቅንብር የተደረገለት ”እውነትም እኛ …” የተባለ ሃያ አምስት ግጥሞች የያዘ ዲቪዲ የግጥም መድብል ቅዳሜ ኅዳር 18 (ኖቬምበር 27) ቀን በስቶክሆልም ከተማ በርካታ ኢትዮጵያውያን በተገኙበት ተመረቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኮሎኔል ታደሰ ሙሉነህ በኤርትራ ፀጥታ ሀይሎች ታፍነው የደረሱበት አልታወቀም

በኤርትራ ያሉ የኢትዮጵያ ታጋዮች ስጋት ላይ ናቸው

Ethiopia Zare (ቅዳሜ ኅዳር 25 ቀን 2003 ዓ.ም. December 4, 2010)፦ የቀድሞ የኢትዮጵያ አየር ሀይል ባልደረባና ከጥቂት አመታት በፊት የአርበኞች ግንባር መስራችና ምክትል ሊቀመንበር፡ የነበረው ኮሎኔል ታደሰ ሙሉነህ፡ ከኦክቶበር 25 ቀን ጀምሮ በአስመራ ከመኖሪያ ቤታቸው ታፍነው ተወስደው መታሰራቸውንና እስካሁንም የደረሱበት እንዳልታወቀ በአስመራ የሚገኙ ምንጮቻችን ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን ቀጥታ ስርጭቱን እንደገና ጀመረ

Ethiopia Zare (ሐሙስ ኅዳር 23 ቀን 2003 ዓ.ም. December 2, 2010)፦ በምህጻረ ቃል ኢሳት (እሳት) በመባል የሚታወቀውና ዋና ቢሮውን በምድረ ሆላንድ ያደረገው የቴሌቪዥን አገልግሎት የቀጥታ ስርጭቱን ዛሬ ማለዳ ላይ በሙከራ መጀመሩን ይፋ አደረገ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኢህአዴግ መንግሥት አቶ ስዩም መስፍንን ወደ ቻይና ላከ

Ethiopia Zare (ሐሙስ ኅዳር 9 ቀን 2003 ዓ.ም. November 18, 2010)፦ ’መተካካት’ በሚል መርኅ የሥልጣን ለውጥ እንደሚያደርግና በአዳዲስና ወጣት ተሿሚዎች እንደሚተካ ቃል የገባው የኢህአዴግ መንግሥት፤ የቀድሞ ቱባ ቱባ ባለሥልጣናቱን በቋሚ ወይንም በባለሙሉ ሥልጣን አምባሣደርነት መሾሙን ካሳወቀ በኋላ፤ ትናንት አቶ ስዩም መስፍንን ወደ ቤጂንግ እንደሚልክ ይፋ አደረገ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አትሌት ኃይሌ ገ/ሥላሴ ወደ ሩጫ መመለሱን አበሰረ

Haile GebreselassieEthiopia Zare (ሰኞ ኅዳር 6 ቀን 2003 ዓ.ም. November 15, 2010)፦ በረዥም ርቀት ውድድሮች ተደጋጋሚ የክብረ ወሰኖች ባለቤት የሆነው ኃይሌ ገብረሥላሴ በድጋሚ ወደ ሩጫ እንደሚመለስ በክብር እንግድነት የተገኘበት ነቀምት ከተማ ህዝብ ፊት በመቅረብ ይፋ አደረገ። ከኒው ዮርኩ ውድድር ነኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በቀጣይ ለሚደረገው የለንደኑ ውድድር ዝግጅቱን እንደሚቀጥልም አብስሯል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በስዊድን የሰማዕታት ቀን ተከበረ

Judge Woldemichael Meshesha, ዳኛ ወልደሚካኤል መሸሻ ”ያወጣው አካል ያላከበረው ሕግ እንዳልተፃፈ ይቆጠራል” ዳኛ ወልደሚካኤል መሸሻ

Ethiopia Zare (ቅዳሜ ኅዳር 4 ቀን 2003 ዓ.ም. November 13, 2010)፦ ከስዊድን በዕለተ እሁድ ከጠዋቱ አራት ሰዓት (10፡00 ሰዓት) ጀምሮ የሚተላለፈው የኢትዮጵያ ድምፅ ሬድዮ የዕለቱን ዝግጅት የጀመረው ’’አይ ሽብሬ” በሚለው ለሰማዕታት ቀን መታሰቢያ በተዘጋጀው ግጥም ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአውሮፓ ህብረት የምርጫ 2002 ዓ.ም. ዝርዝር ሪፖርት አቀረበ

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ጥቅምት 30 ቀን 2003 ዓ.ም. November 9, 2010)፦ ከአምስት ወራቶች በፊት በኢትዮጵያ የተካሄደውንና በወያኔ/ኢህአዴግ 99.6% አሸናፊነት እንደተጠናቀቀ የተገለጸውን ‘ምርጫ’ 2003 በሚመለከት የአውሮፓ ህብረት ታዛቢ ቡድን ዝርዝር ሪፖርቱን አወጣ። ምርጫው ግልጽና ለሁሉም ተቃዋሚዎች የተመቻቸ የመጫዎቻ ሜዳ ማዘጋጀት ያለመቻል ጉድለት ነበረው ሲልም መግለጫው አብራርቷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...