“በወለጋው ግጭት የሞቱት ከ250 ይበልጣሉ” አቶ ቡልቻ ደመቅሣ

“የሞቱት ከ100 አይበልጡም፣ ጥፋተኞች እየተያዙ ነው» የፌ/ጉ/ሚ/ር ሲራጅ ፊርጌሳ

Ethiopia Zare (ሰኞ ሰኔ 2 ቀን 2000 ዓ.ም. June 9, 2008)፦ በምዕራብ ወለጋ በተነሳው ግጭት የሞቱ ሰዎች ብዛት 250 እንደሆነ የተከበሩ አቶ ቡልቻ ደመቅሣ (የኦሮሞ ፌዴራሊስት ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ሊቀመንበር) ለፓርላማው ገለፁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ዶ/ር ብርሃኑ ነጋና ዶ/ር አድማሱ ገበየሁ በሎንዶን ክፍል ፪

"ኢህአዴግ ከዚህ በኋላ አምስት ዓመት ከቆየ በእሱ ጥንካሬ ሳይሆን በእኛ ድክመት ነው" ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ

Ethiopia Zare (እሁድ ሰኔ 1 ቀን 2000 ዓ.ም. June 8, 2008)፦ ዶ/ር ብርሃኑ ነጋና ዶ/ር አድማሱ ገበየሁ በዛሬው ዕለት በሎንዶን ከህዝብ ጋር ባደረጉት ውይይት ላይ ከተሰብሳቢው ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሾች ሰጥተዋል። በዚህ ህዝባዊ ውይይት ላይ ከህዝብ የቀረቡትን ጥያቄዎችና የተሰጡትን ምላሾች በድምፅ እንደሚከተለው አቅርበነዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢ/ር ኃይሉ ሻውል በጋዜጣዊ መግለጫቸው ምን አሉ?

Eng. Hailu Shawel“በሚዲያ የሚደረገው ታንቡርና ጩኸት የህዝብን አስተሳሰብ ይለውጣል ብላችሁ አታስቡ” ኢ/ር ኃይሉ ሻውል

Ethiopia Zare (እሁድ ሰኔ 1 ቀን 2000 ዓ.ም. June 8, 2008)፦ የቀድሞው የቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ፓርቲ ሊቀመንበር የነበሩት ኢንጂንየር ኃይሉ ሻውል ከሀገር ቤት ከወጡ ከዘጠኝ ወራት በኋላ ባለፈው ሣምንት ቅዳሜ ግንቦት 23 ቀን 2000 ዓ.ም. ተመልሰው ወደ ኢትዮጵያ መግባታቸውንና ኀሙስ ግንቦት 28 ቀን መግለጫ መስጠታቸውን መዘገባችን ይታወሳል። የኢ/ር ኃይሉን ጋዜጣዊ መግለጫን አስመልክቶ ከደረሱን ዘገባዎች ውስጥ የሚከተለውን አቅርበነዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አቶ አየለ ጫሚሶ የከሰሷቸው ጋዜጦች አዘጋጆች በክሱ ላይ አስተያየት ሰጡ

“የመንግሥት ሥልጣን ቢሰጣቸው የግል ፕሬሱን ያጠፉት ነበር ማለት ነው?” ዐብይ ተ/ማርያም (አዲስ ነገር)

“በገዥው ፓርቲ እንዲሠሩ የተፈቀደላቸውን ጥቂት ፕሬሶች እሳቸው እያዋከቡት ነው” ዳዊት ከበደ (አውራምባ ታይምስ)

Ethiopia Zare (እሁድ ሰኔ 1 ቀን 2000 ዓ.ም. June 8, 2008)፦ የቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ፓርቲ ሠርተፍኬት ከበርካታ ውዝግብ በኋላ የተሰጣቸው አቶ አየለ ጫሚሶ ሠርተፍኬቱን ካገኙ ገና አንድ ዓመት ሳይሞላቸው ሦስት የግል ጋዜጦች ላይ ክስ መሠረቱ። “የመንግሥት ሥልጣን ቢሰጣቸውና የፖሊስ እና የዐቃቤ ሕግ አካል በእጃቸው ቢገባ ነፃ ፕሬሱን ያጠፉት ነበር ማለት ነው?” ሲል የአዲስ ነገር ማኔጂንግ ኤዲተር ሲጠይቅ፣ “በገዥው ፓርቲ እንዲሠሩ የተፈቀደላቸውን ጥቂት ፕሬሶችን እሳቸው እያዋከቡት ነው” ሲል የአውራምባ ታይምስ ዋና አዘጋጅ አቶ ዳዊት ከበደ አስተያየቱን ሰጥቷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ዶ/ር ፍስኃ እሸቱ ለሁለተኛ ጊዜ ጋዜጣ በተኑ

ኤቢቢአይ ጋዜጣ መታተም አቆመ

Ethiopia Zare (እሁድ ሰኔ 1 ቀን 2000 ዓ.ም. June 8, 2008)፦ የዩኒቲ ዩኒቨርስቲ ኮሌጅ ፕሬዝዳንት በሆኑት በዶ/ር ፍስኃ እሸቱ ባለቤትነት ስር በሚገኘው የሪሊያንስ አፍሪካ ኃ/የተ/የግ/ማኅበር ያሣትመው የነበረው ኤ.ቢ.ቢ.አይ. ዊክሊ የተሰኘው ሣምንታዊ ጋዜጣ መታተም አቆመ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ጠ/ሚ መለስ የኢህአዴግን አቋም ማንም እንደማይቀይረው ገለጹ

"ሚዲያውን በሚመለከት በ1998 ዓ.ም በሰፊው ተተኩሷል፤ ያኔ ያልገደለን የሚዲያ ጥይት አሁን አይገድለንም" ጠ/ሚ መለስ

"የሰጡት አስተያየት የጠ/ሚኒስትሩን አምባገነንነት ቁልጭ አድርጎ ያሳያል" አስተያየት ሰጭዎች

Ethiopia Zare (ዓርብ ግንቦት 29 ቀን 2000 ዓ.ም. June 6, 2008)፦ "የበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማኅበራት ረቂቅ ዐዋጅ" በሚል በተረቀቀው አዲሱ ረቂቅ ዐዋጅን በሚመለከት መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ያደረጉት ውይይት በጠቅላይ ሚኒስትሩ አምባገነናዊ ምላሽ ምክንያት ሊሳካ አለመቻሉን ከአዲስ አበባ የደረሰን መረጃ ጠቆመ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሠራዊቱን ለማጠናከር ከ425 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ተደርጓል

የሠራዊት ምልመላ በሁሉም ክልሎች ሲደረግ በአዲስ አበባ አልተካሄደም

Ethiopia Zare (ዓርብ ግንቦት 29 ቀን 2000 ዓ.ም. June 6, 2008)፦ ከአዲስ አበባ ውጭ በተለያዩ ክልሎች የሠራዊት ምልመላ የተደረገ ሲሆን፣ ከ425 ሚሊዮን ብር በላይ ለሠራዊት ማጠናከሪያ በሚል ሰበብ ወጭ መደረጉን እንዲሁም ከ2ሺ በላይ የሶማሊያ የሽግግር መንግሥት መከላከያ ሠራዊት አባላት እየሠለጠኑ መሆኑ ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢንጂንየር ኃይሉ ሻውል ዛሬ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጡ

Eng. Hailu Shawelስብሰባው በመኢአድ ቢሮ ነበር

"የፖለቲካ ሥራ በጋዜጣ ጡሩንባ በመንፋት አይደለም" ኢንጅነር ኃይሉ

Ethiopia Zare (ኀሙስ ግንቦት 28 ቀን 2000 ዓ.ም. June 5, 2008)፦ ከ9 ወራት በላይ በውጭ ሀገር የነበሩት ኢንጂንየር ኃይሉ ሻውል አዲስ አበባ ከገቡ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ጋዜጣዊ መግለጫ የሰጡ መሆናቸውንና አብረዋቸው ይሰሩ የነበሩ አመራሮችንም መተቸታቸውን የአዲስ አበባ ምንጮቻችን ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ቴዲ አፍሮ ለሰኔ 27 ተቀጠረ

ችሎቱ እንደተለመደው በህዝብ ተጨናንቋል

የችሎቱ ሂደት በባለሙያዎች እየተተቸ ነው

Teddy Afro

Ethiopia Zare (ረቡዕ ግንቦት 27 ቀን 2000 ዓ.ም. June 4, 2008)፦ዛሬ የተሰየመውና ቴዲ አፍሮ የተከሰሰበት ችሎት ብዛት ያለው ህዝብ የተከታተለው ሲሆን፣ 3 ሰዓት ከ30 ላይ የተሰየመው ችሎት ዳኛ ልዑል ገ/ማርያም የዓቃቤ ሕጉን የማስረጃ ዝርዝር መግለጫ እንዲያቀርብ ከጠየቁ በኋላ መጀመሩን የአዲስ አበባ ምንጮቻችን ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...