አቶ ስዬ አብርሃ በኢትዮ-ሱዳን ድንበር ጉዳይ ላይ አቶ መለስን ተቹ
Ethiopia Zare (ማክሰኞ ግንቦት 26 ቀን 2000 ዓ.ም. June 3, 2008)፦ የቀድሞው የመከላከያ ሚኒስትር አቶ ስዬ አብርሃ በኢትዮ-ሱዳን ድንበር ጉዳይ ላይ ያላቸውን አስተያየት ሰጡ። የድንበር ማካለሉን አስመልክቶ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የሰጠውን መግለጫ፣ በተለይም ጠ/ሚ/ር መለስ ዜናዊ ለፓርላማው ግንቦት 13 ቀን 2000 ዓ.ም. የሰጡትን ማብራሪያ አቶ ስዬ አብርሃ ተችተዋል።





