"ለሁሉም ጊዜ አለው" ዳኛ ወልደሚካኤል መሸሻ

Judge Woldemichael Meshesha, ዳኛ ወልደሚካኤል መሸሻ Ethiopia Zare (ረቡዕ መጋቢት 24 ቀን 2000 ዓ.ም. April 2, 2008)፦ የኢህአዴግ አገዛዝን በመቃወምና በተለይም ምርጫ 97ን ተከትሎ ሰኔ 1 ቀን 1997 ዓ.ም. እና ጥቅምት 22 ቀን 1998 ዓ.ም. የኢህአዴግ ታጣቂዎች ካደረሱትን ጭፍጫፋ ጋር በተያያዘ ለስደት የተዳረጉት ዳኛ ወልደሚካኤል መሸሻ በኢትዮጵያ ዛሬ ድረ ገጽ ላይ "የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አስተዳደር በዳይሬክተሩ ታምሷል" በሚል ርዕስ የወጣውን ዜና ተንተርሰው የግላቸውን ምስክርነት ሰጡ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አቶ ዳንኤል እና አቶ ነፃነት ዛሬ ተፈቱ

Ethiopia Zare (ዓርብ መጋቢት 19 ቀን 2000 ዓ.ም. March 28,2008) ከቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ አመራሮች ጋር በቃሊቲ እስር ቤት የነበሩት የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅት አባላት ዳንኤል እና ነፃነት በዛሬው ዕለት ከእስር ቤት የተለቀቁ መሆኑን ከአዲስ አበባ የደረሰን ዘገባ ጠቆመ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አስተዳደር በዳይሬክተሩ ታምሷል

ኮሚቴው ሪፖርት እንዳመለከተው

- በስድስት ሴቶች ላይ ፆታዊ ትንኮሳ ፈፅመዋል፣

- በርካታ ገንዘብ ተመዝብሯል፣

- ከ50 በላይ የቅርብ ቤተሰቦቻቸውን ቀጥረዋል

ልዩ ሪፖርታዥ

Ethiopia Zare (ዓርብ መጋቢት 19 ቀን 2000 ዓ.ም. March 28,2008) ሪፖርተራችን ከአዲስ አበባ የላከልንን እና እንቢልታ ጋዜጣ በዛሬው ዕለት ዓርብ መጋቢት 19 ቀን 2000 ዓ.ም. (ማርች 28 ቀን 2008 እ.ኤ.አ.) ዕትሙ ይዞት የወጣውን ልዩ ሪፖርታዥ ይዘን ቀርበናል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ወ/ት ብርቱካን ወደ ትግራይ ሊጓዙ ነው

Ethiopia Zare (ኀሙስ መጋቢት 18 ቀን 2000 ዓ.ም. March 27,2008) የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች የመስራቾች ፊርማ ለማሰባሰብ በሀገሪቱ በሚገኙ የተለያዩ ክልሎች ሊዘዋወሩ መሆኑን ለፓርቲው ቅርብ የሆኑ የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች ዛሬ ገለጡ። 

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የቀን መቁጠሪያ በማሳተማቸው የተከሰሱትን ፍ/ቤቱ በነፃ አሰናበታቸው

Ethiopia Zare (ኀሙስ መጋቢት 18 ቀን 2000 ዓ.ም. March 27,2008) የቀን መቁጠሪያ በማሳተም አሰራጭተዋል በሚል ተከሰው የነበሩት የአውሮፓ ሕብረት የሕግ ባለሙያዋ፣ የፋንቱ ሱፐር ማርኬት ባለቤት ልጅና አንድ ሌላ ግለሰብ ትናንት በዋለው ችሎት ክሱ እንደተነሳላቸው የፍርድ ቤት ምንጮቻችን ከአዲስ አበባ ገለጡ። 

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአሰቦት ጥንታዊ ገዳም በዚህን ሰዓት እየተቃጠለ ነው

Ethiopia Zare (ኀሙስ መጋቢት 18 ቀን 2000 ዓ.ም. March 27,2008) በኦሮሚያ ክልል የሚገኘውና ረጅም ዕድሜ እንዳስቆጠረ የሚነገርለት የአሰቦት ገዳም የእሳት ቃጠሎ አደጋ ደርሶበት በዚህን ሰዓት እየተቃጠለ እንደሆነ ኢትዮጵያ ያሉ የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች ገለጡ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ዳንኤልና ነፃነት በሽምግልና ሊፈቱ ነው

Ato Daniel & Ato NetsanetEthiopia Zare (ማክሰኞ መጋቢት 16 ቀን 2000 ዓ.ም. March 25,2008) ከቅንጅት አመራሮች ጋር ሕገመንግሥቱንና ሕገመንግሥታዊ ስርዓቱን በኃይል ለማፍረስ ሞክረዋል በሚል ክስ ቀርቦባቸው በእስር ላይ የሚገኙት የሲቪል ማኅበረሰብ አባላት የሆኑት አቶ ዳንኤል በቀለ እና አቶ ነፃነት ደምሴን ከእስር ለማስፈታት የሽምግልና ጥረት መጀመሩን አንድ ታማኝ የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጭ ገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

እነ ዳንኤልና ነፃነት ለመጋቢት 25 ተቀጠሩ

ዛሬ ፍርድ ቤቱ ተጨናንቆ ነበር

Ethiopia Zare (ማክሰኞ መጋቢት 16 ቀን 2000 ዓ.ም. March 25,2008) የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት በእነአቶ ዳንኤልና ነፃነት በኩልና በዓቃቢ ሕግ በኩል በተለያየ መልኩ ቀርቦለት ነበረውን የይግባኝ ጥያቄ በአንድ ላይ ለመጋቢት 25 ቀን 2000 ዓ.ም. እንደሚያይ በስፍራው የተገኘ ዘጋቢያችን ገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ቦርዱ የድጋፍ ደብዳቤ እንደማይጽፍ አስታወቀ

ሰበር ዜና

Ethiopia Zare (ዓርብ መጋቢት 12 ቀን 2000 ዓ.ም. March 21,2008) በወ/ት ብርቱካን የሚመራው ቅንጅት "አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ" በሚል አዲስ ስም ለማቋቋም፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የፊርማ ማሰባሰቢያ የድጋፍ ደብዳቤ እንዲጻፍለት ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያቀረበው ጥያቄ ተቀባይነት አጣ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አቶ አየለ ጫሚሶና ፓርቲያቸው ጋዜጠኞችንና እነወ/ት ብርቱካንን ሊከሱ ይችላሉ

ምርጫ ቦርድ ተባባሪ ነው

Ethiopia Zare (ኀሙስ መጋቢት 11 ቀን 2000 ዓ.ም. March 20,2008) ምርጫ ቦርድ የቅንጅትን ሕጋዊ ሠርቲፊኬት በመስጠት እውቅና የሰጠውና በአቶ አየለ ጫሚሶ ሊቀመንበርነት የሚመራ ፓርቲ፤ ከአሁን በኋላ የቅንጅት የፓርቲ አባል ያልሆኑ ሰዎችን ስለቅንጅት የሚጠይቁ ጋዜጠኞችን እና የፓርቲያቸው አባል ሳይሆኑ በፓርቲው ስም መልስ የሚሰጡትን ግለሰቦች ለመክሰስ ዝግጅቱን እንዳጠናቀቀ የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች ገለፁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...