በሼህ አላሙዲን ሁለት የነዳጅ ማደያዎች ፍንዳታ ተከሰተ

Ethiopia Zare (ሰኞ ሚያዝያ 6 ቀን 2000 ዓ.ም. April 14, 2008)፦ ንብረትነቱ የሼክ መሐመድ ሁሴን አላሙዲንን (በዋናነት)፣ የአቶ አብነት ገ/መስቀል እና የአቶ ታደሰ ጥላሁን የተባሉ አንድ ሌላ ባለሀብት የሆነው ናሽናል ኦይል ኩባንያ (ኖክ) በተባለው ነዳጅ ማደያ ላይ በዛሬው ዕለት ፍንዳ መድረሱን ከስፍራ የደረሰን ዘገባ አስረዳ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢህአዴግ የአንድነት ፓርቲን ፈቃድ ለመከልከል ሕግ አወጣ

“ሕጉ ሆን ተብሎ አንድነት ፓርቲን ለመምታትና ፈቃድ ለመከልከል የተነጣጠረ ነው”

የፖለቲካ ታዛቢዎች

Ethiopia Zare (ቅዳሜ ሚያዝያ 4 ቀን 2000 ዓ.ም. April 12, 2008) ኀሙስ ሚያዝያ 2 ቀን 2000 ዓ.ም. 23ኛ መደበኛ ስብሰባውን ያካሄደው የተወካዮች ምክር ቤት ያፀደቀው የተሻሻለው የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ አዋጅ ኢህአዴግ ለፈለገው ቡድን ብቻ እውቅና ለመስጠት እንዲያስችለው ተደርጎ የተረቀቀ መሆኑ ታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የዳኞች አስተዳደር ጉባዔ "አስተዳደር ዳይሬክተሩን" በሚመለከት ዛሬ ስብሰባ ጠርቷል

Ethiopia Zare (ዓርብ ሚያዝያ 3 ቀን 2000 ዓ.ም. April 11,2008) የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት፣ የፌዴራል ከፍተኛና የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አስተዳደር ዳይሬክተሩ አቶ ዳኛቸው ካሣ በሠራተኞች በቀረበባቸው አቤቱታ መሠረት ጉዳዩን እንዲያጣራ የተቋቋመው ኮሚቴ ያቀረበውን ሪፖርትና የዳኞች አስተዳደር ጉባዔ የደረሰበትን በሚመለከት ለመነጋገር በዛሬው ዕለት ከሰዓት በኋላ በጠቅላይ ፍርድ ቤት ስብሰባ መጠራቱን ለማወቅ ተችሏል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ዶ/ር ያዕቆብና ጋዜጠኛ ዳዊት ክስ ቀረበባቸው

ከሳሽ አቶ አየለ ጫሚሶ ናቸው

Ethiopia Zare (ዓርብ ሚያዝያ 3 ቀን 2000 ዓ.ም. April 11, 2008) ዶ/ር ያዕቆብ ኃይለማሪያምና ጋዜጠኛ ዳዊት ከበደ በአውራምባው ጋዜጣ የካቲት 25 ቀን 2000 ዓ.ም. ቁጥር አንድ ዕትም ላይ ባካሄዱት ቃለምልልስ፤ ዶ/ር ያዕቆብ ቅንጅት አግብብ ባልሆነ መልኩ ለመንገደኛ ተሰጠ ሲሉ በሕጋዊ መንገድ የተሰጠንን ፓርቲ አናንቀዋል ሲሉ አቶ አየለ ጫሚሶ ለፍርድ ቤት ክስ ማቅረባቸውን ዛሬ ከአዲስ አበባ የደረሰና ዘገባ አስረዳ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አንድነት ፓርቲ ከ6 ሺህ በላይ ፊርማ አሰባሰበ

Ethiopia Zare (ኀሙስ ሚያዝያ 2 ቀን 2000 ዓ.ም. April 10,2008) አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲን ለማቋቋም የሚንቀሳቀሰውና በወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ የሚመራው ቡድን ከስድስት ሺህ በላይ ፊርማ አንዳሰባሰበ ለፓርቲው ቅርብ የሆኑ ምንጮች ለኢትዮጵያ ዛሬ ድረ ገጽ ገለጡ። 

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የባሌው ዩኒቨርሲቲ ግጭት ዝርዝር ዘገባ

Ethiopia Zare (ኀሙስ ሚያዝያ 2 ቀን 2000 ዓ.ም. April 10,2008)በትናንት በስቲያ በኦሮሚያ ክልል በባሌ ዞን በሚገኘው ሮቤ ከተማ በሚገኘው የመዳ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ በጎሣና በቋንቋ ምክንያት በተፈጠረ ረብሻ በርካታ ተማሪዎች መጎዳታቸውንና የዩኒቨርስቲውን ቅጥር ግቢ ለቅቀው እስከመውጣት ተገደዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኤሌክትሪክ በፈረቃ መከፋፈል ጀመረ

Ethiopia Zare (እሁድ መጋቢት 28 ቀን 2000 ዓ.ም. April 6,2008) የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን የኤሌክትሪክ ኃይል በፈረቃ ማከፋፈል መጀመሩን በይፋ አስታወቀ። ባጋጠመው የኃይል እጥረት ምክንያት የፈረቃ ፕሮግራሙ ለሚቀጥሉት ሦስት ወራት ይቀጥላል። በአዲስ አበባ የውሃ አገልግሎት እንዳይቋረጥ ለውሃ ፓምፖች ኃይል ማመንጫ በተመረጡ አራት ቦታዎች ላይ የዲዝል ጄነሬተር ተከላ እየተካሄደ ነው። 

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አንድነት ፓርቲ የፊርማ ማሰባሰቡን አገባደደ

Ethiopia Zare (ኀሙስ መጋቢት 25 ቀን 2000 ዓ.ም. April 3,2008) አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲን ፈቃድ ለማግኘትና ለማቋቋም በየክልሉ የመስራቾች ፊርማ ለማሰባሰብ ተሰማርተው የነበሩ የፓርቲው መስራቾች ወደ አዲስ አበባ እየተመለሱ መሆኑን ለፓርቲው ቅርበት ያላቸውና የኢትዮጵያ ዛሬ ድረ ገጽ ምንጮች ገለጡ።

የአርቲስት ደበበ እሸቱ መጽሐፍ በገበያ ላይ ዋለ

Artist Debebe Eshetu's bookEthiopia Zare (ረቡዕ መጋቢት 24 ቀን 2000 ዓ.ም. April 2,2008) የቅንጅት የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ የሆነው አርቲስት ደበበ እሸቱ "የእምነቴ ፈተና" በሚል ርዕስ ያሳተመው መጽሐፍ አሜሪካን ውስጥ ዋሽንግተን ዲሲ ገበያ ላይ መዋሉን ለኢትዮጵያ ዛሬ ድረ ገጽ ቅርብ የሆኑ ወገኖች ጠቆሙ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...