የጥይት ገበያ?

በኮምቦልቻ ከተማ በሕገወጥ መንገድ ለግብይት ቀርበው በቁጥጥር ሥር የዋሉት ጥይቶች

ሁለት ሺሕ የክላሽንኮቭ ጥይት ሲገበያዩ የነበሩ እጅ ከፍንጅ ተያዙ

ኢዛ (ቅዳሜ የካቲት ፳ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. February 27, 2021)፦ ሁለት ሺሕ የክላሽንኮቭ ጥይቶችን በድብቅ ሲገበያዩ የተገኙ ሦስት ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ሥር ማዋሉን የኮምቦልቻ ከተማ ፖሊስ አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአዲስ አበባ ፖሊስ ጣቢያዎች በእጥፍ ሊያድጉ ነው

የዕለቱ የክብር እንግዳ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ሽልማት ሲሰጡ

ለመጪው ምርጫ 2013 ስኬት ከፖሊስ ብዙ ይጠበቃል

ኢዛ (ቅዳሜ የካቲት ፳ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. February 27, 2021)፦ እየተበራከቱ የመጡ ወንጀሎችን ለመከላከል በአዲስ አበባ ከተማ በአሁኑ ወቅት የሚገኙትን የፖሊስ ጽሕፈት ቤቶች በእጥፍ ለማሳደግ ዝግጅት እየተደረገ መኾኑን የአዲስ አበባ አስተዳደር አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ባንኮች 155 ቢሊዮን ብር ብድር ሰጡ

Yinager Dessie (PhD), governor of The National Bank of Ethiopia

ከ110 ቢሊዮን ብር በላይ የሚኾነውን የግሉ ዘርፍ ወስዷል

ኢዛ (ቅዳሜ የካቲት ፳ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. February 27, 2021)፦ ሁሉም የኢትዮጵያ ባንኮች ባለፉት ስድስት ወሮች ከ155 ቢሊዮን ብር በላይ ብድር እንዳሰጡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ዶክተር ይናገር ደሴ ተናገሩ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በኦሮሚያ የፍርድ ቤቶች ትእዛዝ አለመከበሩ እንዳሳሰብው ኢሰመኮ አስታወቀ

Danile Bekele (PHD), Ethiopian Human Rights Commission

ችግሩ ከጊዜ ወደ ጊዜ መባሱንም ዶክተር ዳንኤል ገልጸዋል

ኢዛ (ሐሙስ የካቲት ፲፰ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. February 25, 2021)፦ በኦሮሚያ ክልል ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣው የፍርድ ቤቶች ትእዛዝ አለመከበር እጅግ አሳሳቢ መኾኑን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ለትግራይ ለእርዳታ የመጣን እህል ለመውሰድ የሞከሩ አሥር ግለሰቦች ተያዙ

Shire Town

የእርዳታ እህሉ ለሽሬና አካባቢዋ ነዋሪዎች ሊሰጥ የታሰበ ነው

ኢዛ (ሐሙስ የካቲት ፲፰ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. February 25, 2021)፦ ለትግራይ ክልል ከፌዴራል መንግሥት ለእርዳታ የተላከን እህል በሕገወጥ መንገድ በማውጣት ሊጓጓዝ ሲል መያዙን እና በድርጊቱ የተጠረጠሩት በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሕወሓት በኦሮሚያ ክልል አቅዶት የነበረው ሴራ መክሸፉ ተገለጸ

ጌታቸው ኢታና

በርካታ የሕወሓት አባላት በቁጥጥር ሥር ውለዋል

ኢዛ (ረቡዕ የካቲት ፲፯ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. February 24, 2021)፦ የሕወሓት ቡድን በኦሮሚያ ክልል ውስጥ ትርምስ ለመፍጠር አቅዶት የነበረው ሴራ እንደ ፍላጐቱ አለመሳካቱን የኦሮሚያ ክልል ኃላፊዎች ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ድርድር የሚካሔደው ሱዳን ወደነበረችበት ስትመለስ ነው

Ambassador Dina Mufti

የኢትዮጵያና የሱዳን ውዝግብ ለቀጠናው ሰላም ሥጋት መኾኑ ተገለጸ

ኢዛ (ረቡዕ የካቲት ፲፯ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. February 24, 2021)፦ የኢትዮጵያን ድንበር ጥሶ የገባው እና በኢትዮጵያ ግዛት ክልል ውስጥ ከወራት በላይ የቆየው የሱዳን ጦር ወደ ቀድሞው ይዞታው ከተመለሰ ብቻ ኢትዮጵያ በድንበር ጉዳይ ከሱዳን ጋር ለመደራደር ዝግጁ ስለመኾኗ ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አሳሳቢው ኮቪድ 19 በኢትዮጵያ

Total coronavirus cases in Ethiopia, Feb. 22, 2021

በበሽታው የሚያዙና የሚሞቱ ሰዎች ቁጥር ድጋሚ እየጨመረ ነው
ከሁለት ሺሕ ሰዎች በላይ በበሽታው ሞተዋል

ኢዛ (ሰኞ የካቲት ፲፭ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. February 22, 2021)፦ በኢትዮጵያ በኮቪድ 19 (ኮሮና ቫይረስ) ወረርሽኝ የሚሞቱ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ ስለመምጣቱ እየታየ ነው። በበሽታው ተይዘው ከሚሞቱ ሰዎች ውስጥ የወጣቶችም ቁጥር እንደጨመረ፣ ጽኑ ታማሚዎችም ከወትሮ በተለየ ቁጥር ከፍ እያለ ነው። እስካሁን በበሽታው ተጠቅተው ሕይወታቸው ማለፉ ከተገለጹት ታዋቂ ሰዎች መካከል ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም ይጠቀሳሉ። ትናንት ደግሞ የዓለም ሎሬት ጥበበ የማነብርሃን በዚሁ በሽታ ተይዘው ሕይወታቸው ማለፉን የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል። እንዲህ ካሉ መረጃዎች አንፃር የኮቪድ 19 በሽታ በአሁኑ ወቅት አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን የሚጠቁም ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ