አቶ ገዱ አንዳርጋቸው የአሜሪካን አምባሳደርን ማብራሪያ እንዲሰጡ ጠየቁ

Minister of Foreign Affairs of Ethiopia, H.E. Gedu Andargachew (R) and US ambassador in Ethiopia H.E. Michael Raynor (L), February 13, 2020. (Photo: The Ministry of Foreign Affairs of Ethiopia)

የፕሬዝዳንቱ ንግግር ጦርነት ቀስቃሽ መኾኑን አሳወቁ

ኢዛ (ቅዳሜ ጥቅምት ፲፬ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. October 24, 2020)፦ ፕሬዝዳንት ትራምፕ ግብጽ የህዳሴ ግድብን ታፈነዳለች በሚል የተናገሩትን አወዛጋቢ ንግግር አስመልክቶ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው አዲስ አበባ የሚገኙትን የአሜሪካ አምባሳደር በጉዳዩ ላይ ማብራሪያ እንዲሰጧቸው ጠየቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ትራምፕ ግብጽ የህዳሴ ግድብን ታፈነዳለች ማለታቸው ቁጣን ቀስቅሷል

ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ

ኢትዮጵያውያን በተጠንቀቅ እንዲቆሙ የሚያመላክት መግለጫ መንግሥት አውጥቷል
ኢትዮጵያውያን አቋማቸውን በተለያየ መንገድ እየገለጹ ነው

ኢዛ (ቅዳሜ ጥቅምት ፲፬ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. October 24, 2020)፦ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ግብጽ የታላቋ የህዳሴ ግድብን ያፈነዱታል በሚል ያስተላለፉት መልእክት ውዝግብ እየፈጠረ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ መንግሥትና ኢትዮጵያውያን ንግግሩን በመቃወም አቋማቸውን በተለያዩ መንገዶች እየገለጹ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የትግራይ ክልል ተወካዮች ላይ እርምጃ ሊወስድ ነው

Tafesse Chaffo is the Speaker of the Ethiopian House of Peoples Representatives

የደምወዝ እገዳና የተሰጣቸውን የመኖሪያ ቤት መቀማት ከእርምጃዎቹ ውስጥ ሊኾኑ እንደሚችሉ ተገምቷል

ኢዛ (ረቡዕ ጥቅምት ፲፩ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. October 21, 2020)፦ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ስብሰባ ላይ በማይገኙ የትግራይ ክልል ተወካዮች (የምክር ቤት አባላት) አስተዳደራዊ እርምጃ እንደሚወስድ የምክር ቤቱ አፈ ጉባዔ አስታወቁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ዛሬም አቶ ልደቱ ሊፈቱ አልቻሉም

Lidetu Ayalew

ሕገ መንግሥት በመጣስ የተፈጸመባቸውን በደል አመለከቱ
የዋስትናው ጉዳይ ቀርቶ የፍርድ ሒደቱ ይቀጥል ብለዋል

ኢዛ (ረቡዕ ጥቅምት ፲፩ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. October 21, 2020)፦ ፍርድ ቤት በዋስትና እንዲፈቱ የሰጠው ትእዛዝ ሊፈጸምላቸው ያልቻሉት አቶ ልደቱ አያሌው፤ የዋስትና ጥያቄው ቀርቶ የተከሰሱበት የፍርድ ሒደት እንዲቀጥል መጠየቃጠቸው ተሰማ። አቶ ልደቱ ይህንን ጥያቄያቸውን ያቀረቡት ዛሬ ረቡዕ ጥቅምት 11 ቀን 2013 ዓ.ም. በምሥራቅ ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በቀረቡበት ወቅት ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የወይዘሮ አዳነች አቤቤ ሹም ሽረት

Adanech Abebe

ሰባት የቢሮ ኃላፊዎች በአዲስ ተተክተዋል
ከአሥሩ ክፍለ ከተሞች ሥራ አሥፈጻሚዎች ሦስቱ ብቻ ቀርተዋል

ኢዛ (ማክሰኞ ጥቅምት ፲ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. October 20, 2020)፦ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አፈ ጉባዔ እና ሌሎች ከፍተኛ የከተማው ቢሮ ኃላፊዎችን በአዲስ የተካ ሹመት ተሰጠ። ከአሥሩ የክፍለ ከተማ ሥራ አስፈጻሚዎች ሦስቱ ብቻ ባሉበት እንዲቀጥሉ ተደረገ። ሹመቱን የሰጡትና ያጸደቁት ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ናቸው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ፍርድ ቤቱ አቶ ልደቱ በአስቸኳይ እንዲፈቱ አዘዘ

Lidetu Ayalew

የቢሾፍቱ ፖሊስ ትእዛዙን ባይፈጽም አዛዡ ላይ ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድ አስታወቀ
የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽንም ማብራሪያ እንዲሰጥ ታዟል

ኢዛ (ሰኞ ጥቅምት ፱ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. October 19, 2020)፦ የምሥራቅ ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት አቶ ልደቱ አያሌው ባስቸኳይ እንዲለቀቁና ይህ የፍርድ ቤቱ ትእዛዝ የማይፈጸም ከኾነ አቶ ልደቱን ይዞ በቆየው የቢሾፍቱ (ደብረዘይት) ከተማ ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ላይ ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድ አስታወቀ። የኦሮሚያ ፖሊስም አቶ ልደቱ ታስረው እንዲቆዩ ያደረገበትን ምክንያት ቀርቦ እንዲያስረዳ ትእዛዝ ሰጥቷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአገሪቱ ባንኮች አንድ ትሪሊዮን ብር ተቀማጭ ገንዘብ ሰበሰቡ

PM Abiy Ahmed

ባንኮች ካበደሩት 270 ቢሊዮን ብር 70 በመቶ ለግል ዘርፉ የተሰጠ ነው

ኢዛ (ሰኞ ጥቅምት ፱ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. October 19, 2020)፦ በተጠናቀቀው 2012 በጀት ዓመት በአገሪቱ ታሪክ ከፍተኛ የሚባለውን የአንድ ትሪሊዮን ብር ተቀማጭ ገንዘብ ባንኮች ማሰባሰባቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የ2013 ዓ.ም. 5ኛ ሳምንት አንኳር ወሬዎች

Ethiopia Zare's weekly news digest, week 5th, 2013 Ethiopian calendar

የዓመቱ አምስተኛ ሳምንት አንኳር ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ክንውኖች

ኢዛ (ከጥቅምት 2 - ጥቅምት 8 ቀን 2013 ዓ.ም.) በኢትየጵያ ከሚስተዋለው የፖለቲካ ትኩሳት አንጻር የሚከሰቱ ግጭቶችና ኹከቶች ለዜጐች ሕይወት መጥፋት፣ ንብረት መውደምና የመፈናቀል መንሥኤ የኾኑ ተደጋጋሚ ክስተቶች ታይተዋል። ከጥቂት ወራት ወዲህ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል እየተፈጸመ ያለው አሰቃቂ ድርጊት የወቅቱ የፖለቲካ አጀንዳ ኾኖ ዘልቋል። ባሳለፍነው ሳምንት በዚህ አካባቢ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ የተለያዩ እርምጃዎች እየተወሰዱ ነው። በመከላከያ ሠራዊትና በታጣቂዎች መካከል ከሌላው ጊዜ በተለየ የተኩስ ልውውጥ ተደርጓል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ