ኤርትራ በኤርትራ ተወረረች
ታረቀኝ ሙጬ
እንደማንኛውም ጊዜ ሁሉ የወያኔ ኢሕአዲግን የዜና ማሠራጫዎች - በቀላልና ለሁሉም በሚገባ ቋንቋ የበሬ ወለድ ቱሪናፋ ማራገቢያ ወናፎች ማለትም ይቻላል - እንደአጋጣሚ ሆኖ ከተከታተልኩ ብዙውን ጊዜ ራሴን የምታመምበት አንዳች ነገር አላጣም። በሁለት ሰዓቱ የዛሬ ምሽት ዜና ላይ ለምሳሌ በኢትዮጵያ ድህነት ከ38.7 ወደ 29.6 በመቶ የመቀነሱን ዜና ስሰማ የወትሮ የለበጣ ሣቄም ሳይቀር ከዳኝ። ኑሮው በየቀኑ እየኮደኮደኝ በምን አቅሜ ልሣቅ? ”እዬዬም ሲደላ (ሲዳላ) ነው” መባሉም እኮ ለዚህ ነው። ሣቅም ሆነ ልቅሶ ድሎትን ይሻሉ ማለት ነው።
ሙሉውን አስነብበኝ ...


