የኢትዮጵያ ህዝብ ... ከዚኽ ወዴት? (አያልሰው ደሴ)

የኢትዮጵያ ህዝብ፣ አገር-ወዳድና ዴሞክራሲያዊ ኃይሎች እና ኢህአዴግ፤ ከዚኽ ወዴት? ክፍል አስር

አያልሰው ደሴ (የግል አስተያየት)

በመሆኑም ምንም እንኳን በሁሉም ዘንድ በጎ-ፈቃድ ሊኖር ቢችልም፣ በአንድ በኩል ”ተባባሪ-አባል” በተባሉት (በአብዛኛው ፖለቲካዊ ባልሆኑ ስብስቦች) እና በኢሰዴአኃ፤ በሌላ በኩል ጉባዔውን ባዘጋጁትም ይሁን ኢሰዴአኃን በመሠረቱት ዋና ዋና በተባሉት ”አባላት” እና በኢሰዴአኃ (በአመራሩ) መኻል አለመጣጣሞችና ቅራኔዎች ብቅ ብቅ ማለት ሲጀምሩ ጊዜ አልወሰዱም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ከፌዴሬሽኑ ጀርባ ልንሰለፍ ይገባል

ግርማ ካሣ (ከቺካጎ)

ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ ከቃሊቲ ከተፈታች ሶስት ሳምንታት አልፈዋታል። ከቤተሰቦቿ ጋር ለማሳለፍና በፓርቲዋ እንዲሁም በአገር ቤት ያለውን ሁኔታ የበለጠ ለመመርመር ይረዳት ዘንድ፣ ትንሽ የራሷን ጊዜ በመውሰዷ ለጊዜው ብዙ አንሰማትም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ዴሞክራሲያዊ ኃይሎች ከዚኽ ወዴት? (ክ. ዘጠኝ/አያልሰው ደሴ)

የኢትዮጵያ ህዝብ፣ አገር-ወዳድና ዴሞክራሲያዊ ኃይሎች እና ኢህአዴግ፤ ከዚኽ ወዴት? ክፍል ዘጠኝ

አያልሰው ደሴ (የግል አስተያየት)

በዶ/ር በየነ ጴጥሮስ (የሐድያ ብሔር ዴሞክራሲያዊ ድርጅት) ሰብሳቢነት፣ በአቶ ከበደ ገብራይ (ኢዴኃቅ) ምክትል ሰብሳቢነት እና በዶ/ር ታዬ ወ/ሰማያት (የኢትዮጵያ መምህራን ማኅበር) ፀሐፊነት የተመራውና ከታኅሳስ ፱ እስከ ፲፫ ቀን ፲፱፻፹፮ ዓ.ም. በተካሄደው የአዲስ አበባው ”ሠላምና እርቅ በኢትዮጵያ ሀገር አቀፍ ጉባዔ” ውሳኔ መሠረት በጉባዔው ላይ ከተሳተፉት ውስጥ ሰላሣ አንድ የፖለቲካ ድርጅቶችና የሙያ ማኅበራት በተገኙበት ታኅሳስ ፳፩ ቀን ፲፱፻፹፮ ዓ.ም.የኢሰዴአኃ ምክር ቤትን መመስረታቸው ይታወቃል።

ይሄይስ ተኣምኖ በእግዚአብሔር (ይሄይስ አዕምሮ)

ይሄይስ አዕምሮ

እንደምን ሰነበታችሁልኝ! ባገራችን አንድ አባባል አለ፤ ”ከብቶች እንኳን በየፊናቸው ዱር ውለው ማታ ሲገናኙ ’እምቡዋ’ በመባባል ሠላምታ ይለዋወጣሉ” የሚል። በሌላም በኩል ”እንደከብት ዝም ብለህ አትቀላቀል” የሚለውን ቢፃዊ ግሳጼም ሳንዘነጋ። በ’ርግጥም ነገርን በሠላምታ መጀመር ጥሩ ነው - አሁንም ”ከሺህ ሠላምታ አንድ ሜታ!” ወይም ሦስት ጊዜ ሠላምታ አንዱ ለነገር ነው!” የሚባሉትን ፀረ-ሠላም(ታ) ኃይሎች ማለቴ አባባሎች ሳንረሳ። እናም ሠላምታየ በያላችሁበት ይድረሳችሁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ቀላጤ አርቃቂው ጠ/ሚኒስትር

በዚች ገጠር ወረዳ ብቸኛ ቀላጤ ጸሀፊ የሆነው "አስናቀ ሽቦ" ሰዎች ሲካሰሱ፣ አቤቱታ ሲያቀርቡ፣ ውል ሲፈራረሙ ረቂቅ አዘጋጅቶ በገጽ አንድ ብር እየተቀበለ ቀላጤ ይቸከችካል። ታዲያ ከዕለታት አንድ ቀን በዚያች የገጠር ከተማ ሁከት ይቀሰቀሳል። ... (ሙሉውን ጽሑፍ በፒ.ዲ.ኤፍ. አስነብበኝ!)

በሳውዲ አረቢያ የኢትዮጵያዊያን መከራ (ክፍል አራት)

ነቢዩ ሲራክ - ከሳውዲ ዐረቢያ

በሳውዲ የኢትዮጵያዊያን ሮሮ - የተደበቁ እውነቶች ብየ በጀመርኩት ወጋወግ ዙሪያ ሆኗልና የሚቀድም የሚሰልሰውን አወጣለሁ አወርዳለሁ ... መስከረም በጠባ ማግስት ሌላው ቢቀር ከረመዳን ዋዜማ ጀምሮ በቀጠሉት ቀናት መከራው የበዛባቸውን ወገኖች ውሎ አዳር ለመቃኘት መሞከሬ እውነት ነው! ... (ሙሉውን ጽሁፍ አስነብበኝ!)

የአቶ መለስ ዜናዊ ደብዳቤ

PM Meles Zenawiበሸዋይልማ ኪዳኔ

የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢህአዴግ)

Ethiopian Peoples‘ Revolutionary Democratic Front (EPRDF)

ጉዳዩ፦ የወ/ት ብርቱካንን አፈታት አስመልክቶ የተሰጠ ማብራሪያ

የወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳን ከእስር ቤት በምህረት መለቀቅን አስመልክቶ በቀበሌ፣ በወረዳ እና በዞን ደረጃ በሚገኙ አባላትና ካድሬዎቻችን እንዲሁም በዳያስፖራ በሚገኙ ደጋፊዎቻችን ዘንድ የመንግሥትን እርምጃ በሚገባ አልተረዱም የሚሉ ዘገባዎች በተደጋጋሚ ስለቀረቡልኝ፤ ይህን ደብዳቤ እንደ ጠቅላይ ሚኒስትርነቴ ሳይሆን እንደ ኢህአዴግ ሊቀመንበርነቴ ለመጻፍ ተገድጃለሁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የብርቱካን መፈታት በእናት አይንና በንስር አይን

አለቃ ተክሌ - ከቫንኩቨር-ኦታዋ (ካናዳ)

የ”ሞራል” ብቃትና የሞራል እጥረት ለነገሩ የተፈታው ማነው?

እንዳጋጣሚ ሆኖ ብርቱካንን ለመገምገምና በብርቱካን ላይ የ”ሞራል” ብያኔ ለመስጠት የሚያስችል የ”ሞራል” ብቃት የለኝም። ግን እንደ ባህል ይሄ “አንተ ወይም አንቺ ይሄንን ለማለት ወይም እንዲህ ለመናገር የሞራል ብቃት የለህም/ የለሽም” የሚል መፈክር ደሜን ያፈላዋል። ፖለቲከኞች ላይ የሞራል ፍርድ ለመስጠት የሞራል ብቃት አያስፈልግም። ፖለቲከኞችና ስራቸው እንደ መርህ ለማናቸውም ግምገማና ፍርድ የተጋለጡ ናቸው። ኦባማንና አስተዳደሩን ለመገምገም የአሜሪካ ህዝብ የተለየ የሞራል ብቃት አያስፈልገውም። መንጌ ሃራሬ ቤቱ ቁጭ ብሎ እሱ የሰራውን ቢሆንም እንኩዋን የሚደግመው መለስን መገምገምና ማብጠልጠል ይችላል። ብርቱካንንና ፖለቲካዊ እርምጃዋን ለመገምገም የግድ ለቅጽበትም ቢሆን በቃሊቲ መታሸት የለብንም። በቂ ምክንያት እስካለና በቅን ልቡና እስከተነሳሳን ድረስ የፖለቲካ መሪዎችን መገምገም መብት ነው። እነሆ ከብርቱካን ጉዳይ ጋር በተያያዘ መብቴን ልጠቀም ነው። እንዳጋጣሚ ሆኖ ግን በበጎ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የስደት የፖለቲካ ትግል አጋዥ እንጂ ወሳኝ አይደለም!

ግርማ ካሣ

ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ በቃሊቲ እሥር ቤት እያለች መራራ ስቃይ እንደደረሰባት ሳትደብቅ ደጋግማ ገልጻለች። የቀድሞ የአዲስ ነገር ጋዜጠኛ፣ አብይ ተክለማሪያም፣ የናዚ ጀርመንን ታሪክ በማስታወስ “Verschärfte Vernehmung” (silent Torture) በማለት ለማስረዳት እንደሞከረው፣ አሰቃቂ የስነ ልቦና ቶርቸር እንደተፈጸመባት የሚያከራክርና የሚያወዛግብ አደለም።1

ሙሉውን አስነብበኝ ...