እግር ኳስ ፌደሬሽን ነፃ ይውጣ! (አሸናፊ በቀለ)

አሸናፊ በቀለ

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን፣ በዶ/ር አሸብር ወልደጊዮርጊስ አመራር ስር በነበረበት ወቅት ”… አመራሮቹ ትክክለኛና ፍትሐዊ ውሳኔ የመስጠት ፍላጎትና ችሎታ የላቸውም፣ የሚያስተላልፉት ውሳኔም ሆነ ትዕዛዝ የተወሰኑ ቡድኖችን ሊጠቅም በሚችል ነው፣ ለሥራ ትኩረት አይሰጡም፣ ክለቦች እርስ በርሳቸው እንዲናቆሩ ያደርጋሉ፣ ለአንድ ክለብ ያዳላሉ፣ አምባገነንነት ይታይባቸዋል፣ …” የሚሉ በርካታ ቅሬታዎች ይነሱበት ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ቅና ቢለኝ - በአሜሪካ ምርጫ ቀናሁ (ኃይሌ ታደሰ)

ኃይሌ ታደሰ

የአሜሪካ ምርጫ የዓለም የመገናኛ ብዙኀን ትልቁ አጀንዳ ሆኗል። የትኛውንም የቴሌቭዥን ጣቢያ ቢከፍቱ፣ የኦባማ ንግግር ወይም በየሀገሩ ካሉ የመራጮች ህዝብ ጭፈራና ሆታው ውጭ ምንም ማግኘት አይቻል። በመላ ዓለም ያሉ ራዲዮኖች፣ ጋዜጦች መጽሔቶች፣ ድረ-ገፆች ሁሉም ስለ ኦባማ መመረጥ ይተነትናሉ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

“የኢዴአፓ-መድህን ፖለቲካ የራዕይ ፖለቲካ ነው” ኤርሚያስ ጋሹ

ኤርሚያስ ጋሹ (የኢዴአፓ መድህን ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል)

(”የኢዴአፓ-መድህን የቀውስ ፖለቲካ” በሚል ርዕስ በቃልኪዳን አምባቸው ለቀረበው ጽሑፍ የተሰጠ ምላሽ)

ቃልኪዳን አምባቸው የተባሉ ፀሐፊ ኢዴአፓ-መድህን ፓርቲን አስመልክተው ለሁለተኛ ጊዜ ጽፈዋል። ”የኢዴአፓ-መድህን የቀውስ ፖለቲካ” በሚል ርዕስ ያቀረቡት ይኸው የአቶ ቃልኪዳን ጽሑፍ፤ ቀደም ሲል ለፃፉት ጽሑፍ እኔ የሰጠሁትን ምላሽ መነሻ ያደረገ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ጭፍን ፖለቲካ ይቁም! (ግርማ ካሣ)

በአንድነት ፓርቲ ላይ የተጀመረውን መሰረተ ቢስ ጥቃትን በተመለከተ

ግርማ ካሣ (This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.) - ጥቅምት 20 ቀን 2001 ዓ.ም.

ከዚህ በታች የማቀርበው ሃሳብ የግሌን እንጂ ማንን የፖለቲካ ፓርቲ ወይንም ማኅበር ወክዬ እንዳልሆነ ይታወቅልኝ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኢዴአፓ የቀውስ ፖለቲካ (ቃልኪዳን አምባቸው)

ቃልኪዳን አምባቸው

ኢዴአፓ-መድኅን በቀውስ ፖለቲካ ውስጥ መዘፈቁን የሚያሳዩ በቂ አስረጂዎች አሉ። ፓርቲው ውሉ ጠፍቶበታል። በአንድ በኩል የገዥው ፓርቲ ዕድገት አብሳሪ መሆንን ይሻል። የኢህአዴግን መጠንከር፣ በህዝብ ዘንድ ከፍተኛ ተቀባይነት ማግኘት፣ በመጪው ምርጫ አሸናፊ እንደሚሆንና ሌሎችንም የምንሰማው ከኢህአዴግ የህዝብ ግንኙነት ቢሮ ሳይሆን ከኢዴአፓ-መድኅን የፓርቲዎች የግምገማና የልኬት ቤተ-ሙከራ ነው። ኢዴአፓ-መድኅን ይህን ቢያደርግ በእርግጥ ከልካይ የለበትም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

”የኢቲቪ ግምገማውና ሽልማቱ ይፈተሽ” (ዳግማዊ አልአዛር)

ዳግማዊ አልአዛር

ይድረስ ለፓርላማ

”መልካም አስተዳደር ሽታው እየጠፋ፣

ሙስና ያነቀዘው ሲታይ ሲከረፋ።

በደከሙት ጀርባ ተሸላለሙ አሉ፣

ፓርላማው ይፍረደን … ቦርዶች ዝም ሲሉ።”

”ለኢትዮጵያ ኅዳሴ እተጋለሁ” የሚል አታሞ ከከበሮ እያስደመጠ ባለው ኢቲቪ (የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን) አይሰማ የለም፤ የጽሑፉ መግቢያ የሆነችው ስንኝም የተቃረመችው ከዚያ መሆኑን አስምሩበት።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሦስት ሌሊቶች ከጎዳና ዝሙት አዳሪዎች ጋር

"… ስለውጭ ዜጎች ቀጠለች እቴጌ ”እኛ በጣም ቆንጆዎች ነን፣ ሰውነታችን ከለሩም ቅርፁም ያምራል። በዚህ ላይ በጣም ስለምናስደስታቸውና ንፁኅዎች ስለሆንን ይመስለኛል ዶላራቸውን መዥረጥ እያደረጉ የሚገዙት” እቴጌ ጨዋታዋን ትቀጥላለች። ዝሙት ለሷ የሻጭና የገዥ ጉዳይ ነው፤ የውሀ፣ የመብራት፣ የስልክ፣ የሠራተኛ ግብር … የማይከፈልበት እግዚአብሔር የሰጣት ምርጥ ቢዝነስ ነው። …"

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ከምርጫ 97 በኋላ በተፈጠረው ግጭት የተሳተፉ ሊጠየቁ ይገባል (ፕ/ር ዓለማየሁ ገ/ማርያም)

 ፕሮፌሠር ዓለማየሁ ገ/ማርያም

ባለፈው ሣምንት የኢትዮጵያን ውስጣዊ የፀጥታ ሁኔታ ማዘመን “Moderenizing Internal Security In Ethiopia” የሚል ይፋዊ ሪፖርት ተሰራጭቶ ነበር። ሪፖርቱ በጡረተኛው የብሪታኒያ ኮሎኔል ሚካኤል ዲዋር ሰኔ ወር 2000 ዓ.ም. ላይ የተዘጋጀ ሲሆን ቅኝቱ፣ ግኝቱና የመፍትሔ ሃሳቡ ስኬትን በሚያሳይ መልኩ የተቀመጠ ነው። ለፖለቲካና ኢኮኖሚያዊ ቀውሶችም ምክር ይሰጣል። ኮሎኔል ዲዋር እንደሚገልፁት በጥናቱ ላይ በለንደን የኢትዮጵያ አምባሣደርና በኢትዮጵያ የቀድሞ የብሪታኒያ አምባሳደርን ጨምሮ በርካታ ባለሙያዎች ከግንቦት 2007 እ.ኤ.አ. ጀምሮ መሳተፋቸውን ይጠቅሳል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በሕግ አምላክ! (ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም)

ፕሮፌሠር መስፍን ወልደማርያም - ጥቅምት 2001 ዓ.ም.

በቢሾፍቱ መንገድ አራተኛ ክፍለ ጦርን አልፌ እየነዳሁ ወደመሀል ከተማ እመጣለሁ፤ ትራፊክ መብራቱ ዘንድ በግራ በኩል ዳር ይዤ ቆምሁና አረንጓዴ ሲበራ መንገዴን ቀጠልሁ። በድንገት ከኋላዬ የነበረ ሚኒባስ በቀኝ በኩል በጣም ተጠግቶ ወደግራ ለመታጠፍ ተጠመዘዘ፣ ፍጥነቴን ቀንሼ ላሳልፈው ስል ድንገት ቆመ። አንድ የካድሬ አንደበት ያለው ጎረምሳ ወረደና ወደኔ መጥቶ “መታጠፍ መብቴ ነውኮ!” አለኝ እየተቆጣ፤ በቀኝ በኩል ተጠምዝዞ መቅደም እንዴት መብቱ ሊሆን እንደሚችል በጥሞና ጠየቅሁት። ወደግራ መዞር መብቱ እንደሆነ ደጋግሞ ይነግረኛል። እኔም እንግዲህ የትራፊክ ፖሊስ መጥቶ ይገላግለናል ብዬ አርፌ መኪናዬ ውስጥ ተቀምጬ ቲያትር የማይ መሰለኝ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የትኛው ቡድን ውስጥ ነው ያለነው? (ግርማ ካሣ)

ግርማ ካሣ This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.  ጥቅምት 11 ቀን 2001 ዓ.ም. (October 21, 2008)

ከኢያሪኮ ወደ እየሩሳሌም በሚወስደው መንገድ ላይ እየተጓዘ የነበረ አንድ ሰው፣ በመንገድ ላይ ወንበዴዎች አግኝተውት በሞትና በሕይወት መካከል እስኪሆን ድረስ ደብድበውና ዘርፈውት መንገድ ዳር ጥለውት ሄዱ። ይህ ሰው ባለዕቅድና ባለራዕይ ከቤቱ ሲወጣ ደግሞ ጤነኛ ሰው ነበር። ነገር ግን ያላሰበው ነገር በመንገዱ ላይ አጋጠመው። ቆሞ ይሄድ የነበር ሰው ወደቀ። ጠንካራ የነበረ ሰው ደከመ። በራሱ ይንቀሳቀስና ኪሎ ሜትሮችን ያቋረጥ የነበረ ሰው አንድ እርምጃ መሄድ አቃተው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...