መኢአድና መድረክ በጣት ምልክት ተወዛገቡ

Ethiopia Zare (አርብ ታህሳስ 9 ቀን 2002 ዓ.ም. December 18, 2009)፦ ግንቦት 2002 ዓ.ም. እንደሚካሄድ በሚጠበቀው ምርጫ ለመለያ የሚሆን ምልክታቸውን ካስገቡት የፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል ስምንት ተቃዋሚ ፓርቲዎችን ያቀፈው የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ እና በኢ/ር ኃይሉ ሻውል የሚመራው መኢአድ (የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት) በአውራ ጣት ምልክት ይገባናል ጥያቄ ውዝግብ ውስጥ ገብተዋል። ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኦነግ መግለጫ የሕንድ ባለሀብቶችን አስደነገጠ

Ethiopia Zare (ሰኞ ታህሳስ 5 ቀን 2002 ዓ.ም. December 14, 2009)፦ በቅርቡ በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት ፍቃድ አውጥተው መሬት የተሰጣቸው የሕንድ ባለሀብቶች ሰሞኑን ኦነግ ባወጣው መግለጫ መደናገጣቸውንና ስጋት ላይ መሆናቸው ተሰማ። እሁድ ዕለት አምቦ ከተማ ተረብሻ ዋለች።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአዲስ ነገር ጋዜጣ መዘጋት በአዲስ አበባ አነጋጋሪ ሆኗል

Ethiopia Zare (ሰኞ ታህሳስ 5 ቀን 2002 ዓ.ም. December 14, 2009)፦ ቅዳሜ ኅዳር 26 ቀን የሁለት ዓመት ከወራት ጉዞዋን ያጠናቀቀችውን “አዲስ ነገር” ጋዜጣ ከገበያ መውጣት አስመልክቶ በአዲስ አበባ የተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የሚኖሩ የጋዜጣው አንባቢያንን እንዳስደነገጠ ምንጮች ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ወ/ት ብርቱካንን ለማስፈታት 50 ሺህ ሰዎች በአስር ቀናት ፈረሙ

Write a letter, save a lifeEthiopia Zare (ዓርብ ታህሳስ 2 ቀን 2002 ዓ.ም. December 11, 2009)፦ ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳን ከወህኒ ለማስፈታት የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የሴቶች ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ በአዲስ አበባ ብቻ 50 ሺህ ሰዎች በአስር ቀን ውስጥ ማስፈረሙን ገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኢሰመጉ አባላት ከሀገር እየተሰደዱ ነው

Ethiopia Zare (ዓርብ ታህሳስ 2 ቀን 2002 ዓ.ም. December 11, 2009)፦ ቀድሞ በፕሮፌሠር መስፍን ወ/ማርያም በኋላም በአቶ አበበ ወርቄ ይመራ የነበረውና በመያዶች (NGO) አዋጅ ምክንያት በመፍረስ ላይ ያለው የኢሰመጉ (የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ጉባዔ) አባላት ከሀገር እየወጡ መሆኑ ተሠማ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በግብጽ 17 ኢትዮጵያዊያን በወታደራዊ ካምፕ ታስረዋል

አምስት ሕፃናትና ስምንት ሴቶች ይገኙበታል

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ኅዳር 29 ቀን 2002 ዓ.ም. December 8, 2009)፦ አስዋን ከተማ በሚገኘው ችላል ወታደራዊ ካምፕ ውስጥ 17 ኢትዮጵያዊያን ሁለት ወላጅ አልባ ሕፃናቶችን ጨምሮ ለሁለት ዓመታት በእስር ላይ እየተሰቃዩ መሆኑን ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኢትዮጵያ የሙዚቃና የድራማ ቡድን የመሣሪያ ጨዋታ አሳየ

በማትያስ ከተማ

EMDGB Stockholmደራሲ ገጣሚና ባለቅኔ ኃይሉ ገብረዮሃንስ (ገሞራው) እና ጋዜጠኛ፣ ደራሲና ገጣሚ አበራ ለማ ተገኝተዋል

Ethiopia Zare (ሐሙስ ኅዳር 24 ቀን 2002 ዓ.ም. December 3, 2009)፦ ከሁለት ዓመት በፊት በስዊድን ዋና ከተማ በስቶክሆልም የተቋቋመው የኢትዮጵያ የሙዚቃና ድራማ ቡድን ቅዳሜ ኖቬምበር 28 ቀን ከምሽቱ 12 ሰዓት አንስቶ እስከ እኩለ ሌሊት 6 ሰዓት ድረስ የቆየ በባህላዊ የሙዚቃ መሣሪያ የተቀነባበረ ዝግጅት አቀረበ። በዝግጅቱ ላይ ደራሲ ገጣሚና ባለቅኔ ኃይሉገብረዮሐንስ (ገሞራው) እና ደራሲ፣ ገጣሚና ጋዜጠኛ አበራ ለማ ተገኝተዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...