የታጠቁ ኃይሎች ጥቃት አልቆመም

Protest in Debre Markos, Amhara region

በጅማ እና በደቡብ ክልል በአማሮ ልዩ ወረዳ ታጣቂዎች ንጹኀንን ገደሉ

ኢዛ (እሁድ ሚያዝያ ፲፯ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. April 25, 2021)፦ በጅማ እና በደቡብ ክልል ደግሞ በአማሮ ልዩ ወረዳ የታጠቁ ኃይሎች ሰዎች ስለመግደላቸው እየተገለጸ ሲሆን፤ ግድያው ብሔር ተኮር ስለመኾኑም በጥቃቱ ዙሪያ እየተሠራጩ ያሉት መረጃዎች እያመለከቱ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ምርጫው በተሳካ ሁኔታ ከተከናወነ ለኢትዮጵያ ወርቃማ ድል መኾኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገለጹ

PM Abiy Ahmed

ምርጫው በዚህ ሰዓት መካሔድ የለበትም ብለው መከራከሪያ ለሚያቀርቡ ወገኖች ምላሽ ሰጥተዋል

ኢዛ (እሁድ ሚያዝያ ፲፯ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. April 25, 2021)፦ በኢትዮጵያ የሚካሔደው ምርጫ 2013 በተሳካ ሁኔታ ከተከናወነ ሕዝቦች ወደ ጐዳና መውጣት ሳያስፈልጋቸው በተወካዮቻቸው አማካኝነት ድምፃቸው ስለሚሰማላቸው የዘንድሮው ምርጫ ለኢትዮጵያ ወርቃማ እድል የሚፈጥርላቸው መኾኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ብሔራዊ ደኅንነት ምክር ቤት በሁለት ቢላዎች የሚበሉ የውስጥ ሰዎችን አጸዳለሁ አለ

National Security Council

መግለጫው በሁለት ቢላዋ የሚበሉት አካላትን በግልጽ አልጠቀሰም

ኢዛ (ቅዳሜ ሚያዝያ ፲፮ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. April 24, 2021)፦ በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ የሚመራው ብሔራዊ ደኅንነት ምክር ቤት በየአቅጣጫው የምናየው የወገኖቻችን አሰቃቂ ግድያ፣ ማፈናቀል፣ ቤት እና ንብረት ማውደም፣ ነውጥና ሸፍጥ ሁሉ በአገር ውስጥ ብቻ የተመሠረተ ያለመኾኑን ገልጾ፤ በመጀመሪያ በውስጥ ያሉትን ባለሁለት ቢላዎች እንደሚያጸዳ አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በ10 ቀናት ከ16 ሺህ በላይ የኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎች ተገኙ

Covid 19

የቫይረሱ ተጠቂዎች ቁጥር ሩብ ሚሊዮን ደርሷል
በኮሮና በቀን 28 ሰዎች እየሞቱ ነው

ኢዛ (ቅዳሜ ሚያዝያ ፲፮ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. April 24, 2021)፦ በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ (ኮቪድ 19) በእጅጉ እየተስፋፋ ስለመምጣቱ እየታየ ሲሆን፤ በተለይ ባለፉት አሥር ቀናት ብቻ 16 ሺህ 780 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ሲገኝባቸው፣ 283 ሰዎች ደግሞ በዚሁ ወረርሽኝ ሕይወታቸው አልፏል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የመራጮች የምዝገባ ጊዜ ሊራዘም ነው

Birtukan Mideksa

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከክልል መስተዳድሮች ጋር መክረዋል
ልዩነቶች በጥይት ሳይኾን በምርጫ ካርድ የሚፈቱበት ነው አሉ

ኢዛ (ሐሙስ ሚያዝያ ፲፬ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. April 22, 2021)፦ በተጠበቀው ልክ አለመከናወኑ እየተገለጸ ያለው እና ከነገ በስቲያ የሚጠናቀቀው የመራጮች ምዝገባ ጊዜ እንዲራዘም የፖለቲካ ፓርቲዎችም ጥያቄ ያቀረቡ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የመራጮች ምዝገባ ጊዜውን እንደሚያራዝም አስታውቋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የተቃውሞ ድምፆች መሰማታቸው ቀጥሏል

የአማራ ሕዝብ ተቃውሞ

ባሕር ዳር ፈዝዛ ዋለች

ኢዛ (ሐሙስ ሚያዝያ ፲፬ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. April 22, 2021)፦ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የተፈጸምውን ዘር ተኮር ጥቃት በመቃወም በአማራ ክልል በተለያዩ ከተሞች እየተሰሙ ያሉት ትዕይንተ ሕዝብ ዛሬም በተለያዩ ከተሞች ሲካሔድ ውሏል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አብን በአማራ ላይ የተቃጡት ጥቃቶች ዳግም እንዳይፈጸሙ ማረጋገጥ ያስፈልጋል አለ

National Movement of Amhara (NAMA) and Prosperity party

የአማራ ብልጽግና ፓርቲም መግለጫ አውጥቷል

ኢዛ (ረቡዕ ሚያዝያ ፲፫ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. April 21, 2021)፦ በአማራ ሕዝብ ላይ የተጋረጠው አደጋ ሥርዓትና መዋቅር ሠራሽ በመኾኑ እና የሕዝባችን ትግል የሕልውና ትግል እንደመኾኑ መጠን፤ በሕልውናው ላይ በእቅድና በቅንብር የተከፈቱት ጥቃቶች ዳግም እንዳይፈጸሙ የማረጋገጥ ግቡን እውን ማድረግ አለበት ሲል አብን አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአማራ ክልል ከሰልፍ ያለፈ መፍትሔ ያስፈልጋል አለ

ግዛቸው ሙሉነህ

በአራቱም አቅጣጫ ጥቃት ለመፈጸም ፍላጐት መኖሩንም አስታወቀ
የአንድነት ጥሪ አስተላልፏል

ኢዛ (ረቡዕ ሚያዝያ ፲፫ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. April 21, 2021)፦ ጠላቶቻችን በአማራ ላይ በአራቱም አቅጣጫ ለመፈጸም ፍላጐት ያላቸው በመኾኑ፤ ከሰልፍ የዘለለ መፍትሔ እንደሚያስፈልግ የአማራ ክልል አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢሰመጉ የአገሪቱ ሁኔታ በእጅጉ እንዳሳሰበው አስታወቀ

Ethiopian Human Rights Council

መንግሥት በሕገወጥ መንገድ ታጥቆ የንጹሐንን ሕይወት እየቀጠፈ ባለው ቡድን ላይ ሕጋዊ፣ አስቸኳይ እና የማያዳግም እርምጃ እንዲወስድ ኢሰመጉ ጠይቋል

ኢዛ (ረቡዕ ሚያዝያ ፲፫ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. April 21, 2021)፦ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ውስጥ በተለያዩ አቅጣጫዎች እየተፈጸመ ያለው የሰዎች ሞት፣ አካል መጉደል፣ መፈናቀል እና በአጠቃላይ የሰብአዊ መብቶች ዋስትና ያጡባት አገር መኾኗን በመጥቀስ፤ በአገሪቱ ላይ የተደቀነው ችግር በእጅጉ እንዳሳሰበው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባዔ (ኢሰመጉ) ገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በአማራ ክልል ተቃውሞው አሁንም እየተሰማ ነው

“አማራን መግደልና ማሳደድ ይቁም!”

አጣየ ከተማ በመውደሟ ነዋሪው በድንኳን እየገባ ነው
ሰልፎቹ ሰላማዊ ቢኾኑም አንዳንድ ያልተገቡ ሁኔታዎች መታየታቸውን የአማራ ክልል ኃላፊ ገለጹ

ኢዛ (ረቡዕ ሚያዝያ ፲፫ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. April 21, 2021)፦ ከሚያዝያ 11 ቀን 2013 ዓ.ም. ጀምሮ በአማራ ክልል የተካሔዱ ሰልፎች መንግሥት የዜጐችን ሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች እንዲያስጠብቅና በዘርና በማንነት ላይ ትኩረት ያደረጉ ጥቃቶች እንዲቆሙ መልእክት የተላለፈበት መኾኑን የአማራ ክልል ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ