በደሴ ከተማ ምዕመናንና ፖሊስ ተፋጠዋል፤ መሣሪያ ሲተኮስ ውሎ አንድ መነኩሴ ሞተዋል

ገዢው ፓርቲ ክርስቲያኑንና ሙስሊሙን ማናከሱን ገፍቶበታል

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ሰኔ 23 ቀን 2001 ዓ.ም. June 30, 2009)፦ በደሴ ከተማ የቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን እንድትሠራበት ታቅዶበት የነበረው ቦታ ለረዥም ጊዜ ሲያወዛግብ ቆይቶ፤ የከተማው አስተዳደር ባለሥልጣናት ቦታውን ሙስሊሞች ተቃውመውታል በሚል ሥራው ተቋርጦ በድንኳን ሲቀደስበት ከቆየ በኋላ፤ መንግሥት መልሶ ቦታውን ለሌላ አገልግሎት ይዠዋለሁ በማለቱ ዛሬ በደሴ ከተማ ብዛት ያለው ህዝብ የተሳተፈበት ሠላማዊ ሰልፍ እንደተካሄደና ከሰልፉ በኋላ በምዕመናንና በፌደራል ፖሊሶች መካከል ረብሻ መነሳቱን የዓይን ምስክሮች ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አቶ አበበ ወርቄ በፖሊስ ተይዘው አልቀረቡም

ለሕክምና ወደ ውጭ ሄደዋል ተባለ

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ሰኔ 23 ቀን 2001 ዓ.ም. June 30, 2009)፦ ከአዲስ ብሮድካስቲንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ያለቀረጥ የገቡ የሕትመት መሣሪያዎችን አላግባብ መጠቀም በሚል ክስ ተጠርጥረው ታስረው በዋስ የተለቀቁት እውቁ የሕግ ባለሙያ አቶ አበበ ወርቄ በፖሊስ ተይዘው እንዲቀርቡ ትዕዛዝ ቢወጣባቸውም፤ ዛሬ በዋለው የፍርድ ቤት ውሎ በሕመም ምክንያት ወደ ውጭ ሀገር በመሄዳቸው ሊቀርቡ አለመቻላቸውን የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ማይክል ጃክሰን በ50 ዓመቱ አረፈ

ማይክል ጃክሰን Michael Jackson (Photo: AFP) 

Ethiopia Zare (ዓርብ ሰኔ 19 ቀን 2001 ዓ.ም. June 26, 2009)፦ ይህ ዜና ከመፃፉ ከ7 ደቂቃ በፊት የፖፕ ሙዚቃው ንጉሥ ማይክል ጃክሰን በ50 ዓመቱ ኀሙስ ሰኔ 18 ቀን 2001 ዓ.ም. (June 25, 2009) ማረፉን አሶሺየትድ ፕሬስ ዘገበ። እንደ ዘገባው ከሆነ ለጉዳዩ ቅርበት ያለው ስሙ በይፋ እንዳይገለጽ የፈለገና በኦፊሴል የማይክልን ሕልፈተ ሕይወት ለመግለጽ ያልተፈቀደለት ግለሰብ፤ ማይክል ጃክሰን በሎስ አንጀለስ ሆስፒታል ውስጥ ማረፉን አረጋግጧል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አንድነት መድረክ ጋር የሚያሠሩ ነጥቦች ላይ ውሳኔ ይሰጣል

Ethiopia Zare (ኀሙስ ሰኔ 18 ቀን 2001 ዓ.ም. June 25, 2009)፦ አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ከመድረክ ለምክክር ጋር በጋራ ሊያሠሩ ይችላሉ ተብለው በታመኑባቸው ነጥቦች ላይ በቅርቡ ውሳኔ እንደሚሰጥ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊው ዶ/ር ኃይሉ አርኣያ በተለይ ለኢትዮጵያ ዛሬ ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የግልገል ግቤ 3 ግድብ ውዝግብ እንደቀጠለ ነው

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ሰኔ 16 ቀን 2001 ዓ.ም. June 23, 2009)፦ በአራት የተለያዩ አካላት አጨቃጫቂ እየሆነ በመጣው የግልገል ግቤን የኃይድሮኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ላይ “አሉባልታዎችና ውዥንብሮችን የሚነዛ በህዝብና በሀገር ጥቅም ላይ የተነሳ ነው” ሲል የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት አሳወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሱዳንና ኢትዮጵያ ወታደራዊ ስምምነት አደረጉ

ግብጽ ደስተኛ አይደለችም

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ሰኔ 16 ቀን 2001 ዓ.ም. June 23, 2009)፦ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ወዳጅነታቸው እየጠነከረ የመጣው ኢትዮጵያ እና ሱዳን በወታደራዊ ሥልጠና ዙሪያ ለሦስት ዓመታት የሚቆይ ወታደራዊ ስምምነት በመከላከያ ሚኒስትሮቻቸው በኩል ተፈራረሙ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በያዝነው ዓመት 12 የጐሣ ግጭት መከሰቱን ፖሊስ አመነ

Ethiopia Zare (ዓርብ ሰኔ 5 ቀን 2001 ዓ.ም. June 12, 2009)ሀገሪቱን ብሔር ብሔረሰቦች ሸንሽኖ በሚገዛው በኢህአዴግ መንግሥት አስተዳደር ውስጥ 10 ወራት ብቻ 12 ብሔር ብሔረሰቦችና የጐሳ ግጭቶች በኢትዮጵያ ተከስቶ እንደነበር የፌዴራል ፖሊስ ዋና ዳይሬክተር አቶ ወርቅነህ ገበየሁ አሳወቁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ፕሮፌሠሩ በህወሓት ሰዎች ተተቹ

Ethiopia Zare (ዓርብ ሰኔ 5 ቀን 2001 ዓ.ም. June 12, 2009)፦ በአሜሪካን ሀገር “The Ethiopian Revolution war in the Horn of Africa” በሚል ርዕስ መጽሐፍ ጽፈው ያሰራጩት ፕሮፌሠር ገብሩ ታረቀ ባለፈው ሣምንት በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የኢህአዲግ ባለሥልጣናትና ጄኔራሎች በተገኙበት ስብሰባ በህወሓት ሰዎች ትችት ቀረበባቸው። ሙሉውን አስነብበኝ ...