የባሥልጣናት የሹም-ሽር በመስከረም ማግስት ይካሄዳል ተባለ

Ethiopia Zare (ረቡዕ ሐምሌ 8 ቀን 2001 ዓ.ም. July 15, 2009)፦ በአዋሳ ከተማ ከ10 ወር በፊት በተካሄደው የኢህአዲግ ጠቅላላ ስብሰባ ድርጅቱን በወጣት አመራር እገነባለሁ ያለው ገዥው ፓርቲ በመጪው መስከረም የህወሓት ኢህአዲግ ጠቅላላ ጉባዔ በኋላ ጡረታ የሚወጡ የድርጅቱ አንኳር ሰዎች መኖራቸው ተጠቆመ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ዛሬ ቅዱስ ሲኖዶስ ጉባዔ ተቀምጧል

የመንግሥት ባለሥልጣኖች በታዛቢነት ታድመዋል

Ethiopia Zare (አርብ ሐምሌ 3 ቀን 2001 ዓ.ም. July 10, 2009)፦ እየተካረረ የመጣውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋኅዶ ቤተክርስቲያን የጳጳሳት ውዝግብ ለመፍታት በማሰብ የተጠራው የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባዔ፤ ዛሬ አርብ ሐምሌ 3 ቀን 2001 ዓ.ም. የመንግሥት ሁለት ከፍተኛ ባለሥልጣኖች በተገኙበት ማለዳ ላይ በቅዱስ ፓትርያርኩ ጽ/ቤት የመሰብሰቢያ አዳራሽ መካሄድ ጀምሯል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አንጋፋው አርቲስት ዓለሙ ገብረአብ አረፈ

 አርቲስት ዓለሙ ገብረአብ Alemu Gebreabዛሬ አርብ ሥርዓተ ቀብሩ ተፈጸመ

Ethiopia Zare (አርብ ሐምሌ 3 ቀን 2001 ዓ.ም. July 10, 2009)፦ አንጋፋው ከዚህ አለም በሞት መለየቱንና ዛሬ ዕለተ አርብ ሐምሌ 3 ቀን 2001 ዓ.ም. ከቀኑ 6 ሰዓት ከ30 በየካ ሚካኤል ቤተ-ክርስቲያን መካነ-መቃብር ሥርዓት ቀብሩ መፈጸሙን የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች አረጋገጡ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አቶ በረከት በፕላዝማ ለመምህራን አብዬታዊ ዲሞክራሲን ሰበኩ

መምህራን ፍላጐታቸው የትምህርት ጥራትና ኑሮን ያገናዘበ ደሞዝ ማግኘት መሆኑን አሳወቁ

Ethiopia Zare (ቅዳሜ ሰኔ 27 ቀን 2001 ዓ.ም. July 4, 2009)፦ ሰኔ 21 ቀን ከጠዋቱ 2 ሰዓት ተኩል በኋላ መምህራን ወደ አጋርፋና ፍቼ እንደዚሁም ሌሎች አካባቢዎች ለፖለቲካዊ ንቃት ከተንቀሳቀሱ ወዲህ ሰኞ ሰኔ 22 ቀን 2001 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማም ጭምር የተጀመረው የአብዮታዊ ዴሞክራሲ፣ የልማታዊ መንግስት እና የፍትሃዊ ሥርዓት ትምህርት በዛሬውም እለት ቀጥሎ ውሏል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ከአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ ከ500 የሚበልጡት እንደሚባረሩ ተገለጸ

Ethiopia Zare (ቅዳሜ ሰኔ 27 ቀን 2001 ዓ.ም. July 4, 2009)፦ በጦላይ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ማዕከል ከተካሄደው 3ኛ ዙር የሥነ-ምግባር ነክ ግምገማ በኋላ፣ ከአዲስ አበባ ከተማ የፖሊስ ሠራዊት ባለደረቦች መካከል ከ500 የሚበልጡት “ይባረራሉ፣ በሂስና በግለ-ሂሱ መድረክ ወንጀል ስለመፈጸማቸው ያመኑትና ምስክር የቆመባቸው ፖሊሶች የክስ ፋይል ይከፈትባቸዋል” ተባለ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የፓትርያርኩና የጳጳሱ ሽኩቻ ተባብሷል

“ቃለ ዓዋዲው ይዳኛችሁ” ጠ/ሚ መለስ

Ethiopia Zare (ቅዳሜ ሰኔ 27 ቀን 2001 ዓ.ም. July 4, 2009)፦ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በፓትርያሪኩና በአቡነ ሳሙኤል መካከል ተከስቶ የነበረው ግጭት መባባሱንና ባለፈው ማክሰኞ ስብሰባ የቤተክህነት ውዝግብ መቀጠሉ ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አትሌት ቀነኒሳ፣ መሰረት እና ደረሰ በኦስሎው ጎልደን ሊግ አሸነፉ

Meseret Defar አትሌት መሰረት ደፋርKenenisa Bekele አትሌት ቀነኒሳ በቀለEthiopia Zare (አርብ ሰኔ 26 ቀን 2001 ዓ.ም. July 3, 2009)፦ በያዝነው የአውሮፓውያን 2009 እየተካሄደ ባለው የኤ.ኤፍ. ጎልደን ሊግ አትሌቲክስ በ5 ሺህ ሜትር ርቀት አትሌት ቀነኒሳ በቀለ እና መሰረት ደፋር በኖርዌይ ዋና ከተማ ኦስሎ ውድድሩን በአንደኝነት አጠናቀቁ። የጎልደን ሊጉን አንድ ሚሊዮን ዶላር ሽልማት ይቋደሳሉ ተብለው ከሚጠበቁት አትሌቶች ውስጥ ሁለቱ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ይገኙበታል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አንድነት በደብረማርቆስ የተሳካ ስብሰባ አካሄደ

“አቶ ስዬ አብርሃ አንድነትን ለመቀላቀል ጥያቄ አላቀረቡም፤ ማመልከቻም አላስገቡም” ዶ/ር ኃይሉ አርኣያ

Ethiopia Zare (አርብ ሰኔ 26 ቀን 2001 ዓ.ም. July 3, 2009)፦ አንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ ባለፈው እሁድ በደብረ ማርቆስ ከተማ ያካሄደው ስብሰባ ብዙ ፈተናዎች ቢያጋጥሙትም በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁ ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በደሴ የሟቾች ቁጥር አራት ደርሷል፤ የቁስለኞችም ቁጥር አሻቅቧል

አባ ጳውሎስ ከ“ሕገ-ወጦች ጋር” አናብርም አሉ

Ethiopia Zare (ረቡዕ ሰኔ 24 ቀን 2001 ዓ.ም. July 1, 2009)፦ በደሴ ከተማ ፌደራል ፖሊሶች በክርስትና እምነት ተከታዮች ላይ በወሰዱት የጭካኔ እርምጃ ምክንያት የሞቱ ሰዎች ቁጥር ከሁለት ወደ አራት ከፍ ብሏል። ከስፍራው በተቃውሞ ሰልፉ የተሳተፈች ሴትና የፖሊስ ዱላ ያረፈባት ሴት እንደገለጸችልን ከሆነ አንዱ ሟች ከላሊበላ የመጣ በስንቅ የሕክምና ትምህርት የሚከታተል ወጣት ሲሆን፤ አስከሬኑ ወደቤተሰቦቹ መሄዱን ገልጻለች።

ሙሉውን አስነብበኝ ...