ኢትዮጵያ በ10 ምርጦች
Ethiopia Zare (ቅዳሜ መስከረም ፲፯ /17 ቀን ፳፻፩/2001 ዓ.ም. September 27, 2008)፦ ኢትዮጵያን በመጥፎም ሆነ በበጐ ጐን ከዓለም አስር ሀገራት ተርታ የሚያሰልፏት ሩሴል አቮ የተባሉ ደራሲ (Top 10 of everything 2009) በሚል መጽሐፋቸው ያሰፈሯቸው ጉዳዮች አንዳንዶቹ የሚታወቁ ሌሎቹ ደግሞ ፈጽሞ የማይታወቁ አስገራሚ ነገሮች ናቸው። ለምሣሌ የዓለማችን ዋነኛ ሞቃት ሥፍራ ዳሎል በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኝ ሲሆን፣ 94.3 ዲግሪ ፋራናይት ወይም 34.6 ዲግሪ ሴንቲግሬድ ሙቀት እንዳለው በመጽሐፉ ላይ ተጠቅሷል፤ ከዳሎል ቀጥሎ በሞቃታማነቱ የተጠቀሰው በኤርትራ የሚገኘው አሰብ ነው።
ሙሉውን አስነብበኝ ...

"ክቡር ሊቀመንበር ምንም እንኳን እናንተ የአጼውና የካቢኔው ወንበር ቢሞቃችሁም እኛን ግን የፓርላማ ወንበር ለመውረስ የተወከልን ሳንሆን በአቧረ አቤታችን ተሰብስበን የሰራተኛውን ጉዳይ እንድንወያይ ቤታችን እንዲከፈትልን ነው ጥያቄያችን" አቶ ሹምዬ ተፈራ በደርግ መሪ ፊት የተናገሩት 


