ኢዜማ በምርጫው ባጋጠሙን ችግሮች ላይ ምርጫ ቦርድ ውሳኔ የማይሰጥ ከኾነ ፍ/ቤት እሔዳለሁ አለ

Ethiopian Citizens for Social Justice

ፓርቲው ነገም ቀጣይ ፓርቲ ኾኖ የሚዘልቅ ስለመኾኑ ገልጿል

ኢዛ (ሐሙስ ሰኔ ፲፯ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. June 24, 2021)፦ ባለፈው ሰኞ ሰኔ 14 ቀን በተካሔድው ምርጫ 2013፣ ኢዜማ በተወዳደረባቸው በርካታ የምርጫ ክልሎች ያጋጠሙትንና ለምርጫ ቦርድ ያሳወቃቸውን በርካታ ተግዳሮቶችን ተመልክቶ ውሳኔ የማይሰጥባቸው ከኾነ ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት እንወስዳለን አለ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢትዮጵያ ባለድርሻ የኾነችበት የበርበራ ወደብ ተርሚናል ሥራ ጀመረ

ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ፣ አቶ አሕመድ ሸዴ፣ ፕሬዝዳንት ሙሳ ቢሂ አብዲ፣ የዲፒ ወርልድ ዳይሬክተር ሱልጣን ቢን ሱለይማን እና አቶ ሙስጠፌ መሐመድ (ከግራ ወደቀኝ)

ኢትዮጵያ 19%፣ ሶማሌላንድ 30% እና ዲፒ ወርልድ 51% ድርሻ አላቸው

ኢዛ (ሐሙስ ሰኔ ፲፯ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. June 24, 2021)፦ በሶማሌላንድ በርበራ ወደብ በኢትዮጵያ አሥራ ዘጠኝ በመቶ የባለቤትነት ድርሻ የተያዘው የበርበራ ተርሚናል ኮሪደርና የመጀመሪያ ዙር ማስፋፊያ ፕሮጀክት ተጠናቆ አገልግሎት ጀመረ። ቀሪው ድርሻ 30 በመቶ የሶማሌላንድ ሲሆን፣ 51 በመቶ ደግሞ የዲፒ ወርልድ እንደኾነ ታውቋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ብልጽግና ምርጫውን ሲገመግም፤ ኢዜማ በምርጫው ሒደት ላይ መግለጫው ይጠበቃል

ምርጫ 2013

ኢዜማ ድምፅ መስጠቱ ከተጠናቀቀ በኋላ የምርጫ ሒደቱን በተመለከተ የመጀመሪያውን መግለጫ የሚሰጥ ፓርቲ ይኾናል

ኢዛ (ረቡዕ ሰኔ ፲፮ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. June 23, 2021)፦ የብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ስድስተኛውን አገር አቀፍ ምርጫ 2013 ሒደት የተመለከተ ግምገማ ማድረጉን ሲያሳውቅ፤ ኢዜማ አጠቃላይ የምርጫውን ሒደት በተመለከተ መግለጫ እንደሚሰጥ ገልጿል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ለወራት ተቋርጦ የነበረው የአስመራ በረራ ዳግም ተጀመረ

Ethiopian Airlines

በረራውን አቋርጦ የነበረው በትግራይ ክልል ከተፈጠረው ጦርነት ጋር የተያያዘ እንደኾነ ይታመናል

ኢዛ (ረቡዕ ሰኔ ፲፮ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. June 23, 2021)፦ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለወራት አቋርጦት የነበረውን የአስመራ በረራ ዛሬ ረቡዕ ሰኔ 16 ቀን 2013 ዓ.ም. በድጋሚ መጀመሩን አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢትዮጵያ ከፈረንሳይና ከጣሊያን ጋር በመከላከያ ዙሪያ ለመሥራት የሚያስችል ረቂቅ አዋጅ ለፓርላማ ተላከ

98ኛ መደበኛ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ ውሳኔዎች

የመለስ አካዳሚ ስያሜ እንዲቀየር የሚኒስትሮች ምክር ቤት ወሰነ

ኢዛ (ማክሰኞ ሰኔ ፲፭ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. June 22, 2021)፦ ኢትዮጵያ ከጣሊያን እና ከፈረንሳይ ጋር በመከላከያ ዙሪያ በጋራ ለመሥራት ያደረገቻቸውን የሁለትዮሽ ስምምነቶች ሕጋዊ ማዕቀፍ እንዲኖረው የሚያደርገውን የማጸደቂያ ረቂቅ አዋጅ እንዲጸድቅ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተላከ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የምርጫ ውጤቱን ወደ አዲስ አበባ ለማስመጣት ምርጫ ቦርድ ትብብር ጠየቀ

Ballot box, Ethiopian Election 2021

ለጸጥታ ኃይሎችና ለሹፌሮች ቦርዱ አበል ይከፍላል

ኢዛ (ማክሰኞ ሰኔ ፲፭ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. June 22, 2021)፦ ስድስተኛው አገር አቀፍ ምርጫ ትናንት በሰላም መጠናቀቁ ከተገለጸ ወዲህ፤ የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ የምርጫ ውጤቶችን ከክልል ወደ አዲስ አበባ በልዩ ጥበቃ እንዲገቡ የክልል መንግሥታትን ጠየቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የምርጫው አንደምታ በጨረፍታ

ምርጫ 2013

- ምርጫ 2013 በሰላም እየተካሔደ ነው
- የፖለቲካ ድርጅቶች ምልከታ
- በአንዳንድ አካባቢዎች ችግሮች እየሰማን ነው ያሉም አሉ

ኢዛ (ሰኞ ሰኔ ፲፬ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. June 21, 2021)፦ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎችን የሚወዳደሩ እጩዎች ውስጥ ብዙዎች በማለዳ ድምፅ ሰጥተዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ወ/ት ብርቱካን መመሪያ እንዲሰጥበት ያሳሰቡበትን ጥያቄ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ላኩ

ወ/ር ብርቱካን ሚደቅሳ ለዶ/ር ዐቢይ አሕመድ የጣፉት ደብዳቤ

ፈጣን ምላሽ የሚሰጥ የሕግ አስፈጻሚ ኃይል ያስፈልጋል ብለዋል

ኢዛ (ቅዳሜ ሰኔ ፲፪ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. June 19, 2021)፦ ስድስተኛውን አገራዊ ምርጫን (ምርጫ 2013) ሰላማዊነት ለማረጋገጥ ተጠባባቂ የሕግ አስፈጻሚ ኃይል የምርጫ ቦርድ ለሚጠይቃቸው ጥያቂዎች ፈጣን ምላሽ እንዲሰጡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ መመሪያ እንዲያስተላልፉ የምርጫ ቦርድ ጠየቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጦር መሣሪያ ያጓጉዛል መባሉን አስተባበለ

Ethiopian Airlines

አየር መንገዱ በማንም የጦር መሣሪያ የማጓጓዝ አገልግሎት ተጠይቆ እንደማያውቅ ገልጿል

ኢዛ (ዓርብ ሰኔ ፲፩ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. June 18, 2021)፦ በአፍሪካ ቀዳሚ የአየር ትራንስፖርት በመስጠት የሚታወቀው አንጋፋው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቅርቡ የጦር መሣሪያ ያጓጉዛል በሚል ቀርቦብኛል ያለውን ትችት ሐሰት ነው አለ። አየር መንገዱ በግለሰብም ኾነ በተቋም ደረጃ የጦር መሣሪያ የማጓጓዝ አገልግሎት ተጠይቆም እንደማያውቅ ገልጿል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኤርትራ ወታደሮች እየወጡ ነው

Eritrean flag

ከትግራይ አካባቢዎች ተንቀሳቅሶ ወደ ኢትዮ-ኤርትራ ድንበር መመለስ መጀመሩ ተዘገበ

ኢዛ (ሐሙስ ሰኔ ፲ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. June 17, 2021)፦ የሕወሓት ቡድን በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ላይ የፈጸመውን ጥቃት ተከትሎ በተቀሰቀሰው ጦርነት ወደ ኢትዮጵያ ገብቶ የነበረው የኤርትራ መከላከያ ሠራዊት ከኢትዮጵያ ግዛት መውጣት መጀመሩ ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ