የጋዜጠኞችና የጋዜጦች ህልውና አደጋ ላይ ነው

የአንድ ጋዜጣ ዋጋ 7ብር ገብቷል

Ethiopia Zare (ሐሙስ ሚያዝያ 13 ቀን 2003 ዓ.ም April 21, 2011)፦ ሰሞኑን በጋዜጦችና በጽሔቶች ላይ የተደረገው የዋጋ ጭማሪ በርካታ ጋዜጦችንና ጋዜጠኞችን ከስራ ውጭ እንደሚያደርጋቸው እና የህትመት ስራ በአጠቃላይ ከፍተኛ አደጋ ውስጥ መሆኑ ተገለጸ።

 

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ለኢሳት ገንዘብ ማሰባሰቢያ ዝግጅት በኦታዋ

Ethiopia Zare (ሐሙስ ሚያዝያ 13 ቀን 2003 ዓ.ም April 21, 2011)፦ በካናዳ ዋና ከተማ ኦታዋ በያዝንው ወር ቅዳሜ ሚያዚያ 30 ቀን ለኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቭዥን ማጠናከሪያ የሚሆን የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ፣ አርቲስት ታማኝ በየነና የተለያዩ የካናዳ የፖለቲካ ሰዎች በተገኙበት እንደሚካሄድ ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በቃ! ገዬ! በስ! አሎኒ! ጊደስ!

Beqa! Sweden, Stockholm April 08, 2011በስዊድን የኢትዮጵያውያን የሰልፍ ውሎ

Ethiopia Zare (ቅዳሜ ሚያዝያ 1 ቀን 2003 ዓ.ም April 9, 2011)፦ ትናንት ዓርብ መጋቢት 30 ቀን 2003 ዓ.ም. ትንሽ ትንሽ፣ ብን ብን ከሚለው ዝናብ በስተቀር ይሄን ያህል ብርድ አልነበረም። የስዊድን ክረምት (ዊንተር) ከመቼውም በበለጠ ሁኔታ እንኳን ለስደተኛው ለዜጋውም አልገፋ ብሎ በረዶው በአንዳንድ ከተሞች ከመሬቱ አልላቀቅ ብሎ ሙጭጭ ያለበት ዓመት ነው - የአውሮጳውያኑ 2011። የአየሩ ፀባይ አፈር ሲሉት ውሃ እንደሆነ የሚያውቀው ኢትዮጵያዊ ግን የክረምት ልብሱን አልወጠም። በሻርፕ ተጠቅሏል፤ ኮፍያውንም አልጣለም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በአደስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተቃውሞ ሰልፍ ጥሪ ወረቀት ተበተነ

በኦሮሞ ተወላጆች ላይ እስራቱ ቀጥሏል

Ethiopia Zare (አርብ መጋቢት 16 ቀን 2003 ዓ.ም. March 25, 2011)፦ ከእረፍት በኋላ ወደ ትምህርት ገበታቸው ለተመለሱ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ሰኞ ጠዋት የተቃውሞ ሰልፍ እንዲወጡ የሚጠይቅ በራሪ ጽሁፍ በግቢው ውስጥ መበተኑን ምንጮች ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች አመጽ ሊያስነሱ እንደሚችሉ ተነበየ

በእረፍት ላይ የሰነበቱት ተማሪዎች ወደግቢ እየተመለሱ ነው

ጠንካራ ፖለቲካዊ ጽሁፎችን በመጻፍና ድፍረት የተሞላባቸውን ሀሳቦች በማስተጋባት የሚታወቀው፡ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፡ ከእረፍት እየተመለሱ ያሉት የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች እንደ ግብጽና ቱኒዚያ አጋሮቻቸው የኢትዮጵያን ፖለቲካዊ ሁኔታ ሊቀይር የሚችል አመጽ ሊያስነሱ እንደሚችሉ ተነበየ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ በኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ማብራሪያ ሊሰጥ ነው

Ethiopia Zare ( ቅዳሜ መጋቢት 3 ቀን 2003 ዓ.ም. March 12, 2011)፦ ሚኒሊክ፣ አስኳልና ሳተናው በተባሉት ጋዜጦቹ የሚታወቀውና በአሁኑ ሰዓት በህትመት ስራ ላይ እንዳይሳተፍ የታገደው ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፤ በተለይ ለአቶ መለስ ዜናዊ በጻፈው ግልጽ ደብዳቤና በወቅታዊ የኢትዮጵያ ጉዳዮች ዙሪያ በሬዲዮ ውይይት እንደሚያደርግ ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ስኳርና ዘይት ከገበያ መጥፋት አሳሳቢ ሆኗል

የትራንስፖርት እና የነዳጅ ዋጋ እያሻቀበ ነው

Ethiopia Zare (አርብ መጋቢት 2 ቀን 2003 ዓ.ም. March 11, 2011)፦ የዋጋ ማስተካከያ የተደረገባቸው ሸቀጣ ሸቀጦች በአብዛኞቹ ከገበያ መጥፋታቸውና በተለይ ስኳርና ዘይት በገበያ ላይ ማግኘት አስቸጋሪ መሆኑን ሸማቾች ገለጹ። በመጓጓዣ ዋጋ ላይ እስከ 1 ብር ከ95 ሣ. ጭማሪ ተደርጓል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የቴሌ ኮሙኒኬሽን ሰራተኞች ሮሮ መልስ አላገኘም

ስምንት ሺህ የሚደርሱ ሰራተኞች ተባረዋል

Ethiopia Zare (ረቡዕ የካቲት 23 ቀን 2003 ዓ.ም. March 2, 2011)፦ የኢትዮጵያ ቴሌ ኮሞኒኬሽን አስተዳደር ፈርሶ በፈረንሳዩ ፍራንስ ቴልኮም ቁጥጥር ስር እንዲገባ ከተደረገ ጀምሮ ስምንት ሺህ የሚደርሱ የቴሌ ሰራተኞች ከተባረሩ በኋላ የሚያሰሙት ሮሮ ተቀባይነት እንዳላገኘ ምንጮች ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የደራሲ አበራ ለማ ታሪካዊ ልብ-ወለድ መጽሐፍ በአዲስ አበባ ተመረቀ

Tilo malef, ጥሎ ማለፍማትያስ ከተማ (ከስዊድን)

Ethiopia Zare (ሐሙስ የካቲት 17 ቀን 2003 ዓ.ም. February 24, 2011)፦ ”ጥሎ ማለፍ” የተሰኘው የአንጋፋው ጋዜጠኛና ደራሲ አበራ ለማ አዲስ ልብ-ወለድ መጽሐፍ እና በቅርቡ የወጣው ”እውነትም እኛ ...” የተሰኘው የግጥም ዲቪዲ የካቲት 12 ቀን 2003 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ተመረቁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...