ብርቱካንን እንጂ ዓላማውን ማሰር አይቻልም!!!

በስዊድን የተካሄደ ብርቱካን ትፈታ ህዝባዊ ስብሰባ

ስሜነህ ታምራት - ከስዊድን

Stockholm 2010, 02, 20 Free Birtukan!

የመሰብሰቢያ አዳራሹ በኢትዮጵያና በስዊድን ሰንደቅ ዓላማዎች ከብርቱካን ፎቶግራፍ ጋር ተውበዋል። ወደ ውስጡ ሲገባ ብርቱካን ቃሌ ብላ ከሰጠችው የተወሰደው የእውነተኛ ምስክርነት ንግግርና ለእስር ምክንያት ተብሎ የቀረበው በስዊድን ጉብኝትዋ ስለምህረቱ አፈፃፀም ያደረገችው ንግግር ይሰማል። በተለያዩ ሀገሮች ከህዝብ ጋር ስትወያይ ”ባገራችን ሠላም ዲሞክራሲና የሕግ የበላይነት እንዲከበር እኔ በዓላማዬ ፅኑ ነኝ እናንተስ?” በማለት ያስተላለፈችውና በማንኛውም ሐቀኛ ዜጋ ዘወትር የማይረሳው የቆራጥነት መንፈሧ በአየር ላይ ይታያል። ሙሉውን አስነብበኝ ...

በስዊድን ወ/ሪት ብርቱካን የሚታሰቡበት ታላቅ ህዝባዊ ስብሰባ ይካሄዳል

ቫኛ ሉንድቢ ቬዲን (የአውሮፓ የሠራተኞች ማኅበር ፕሬዝዳንት)ቫኛ ሉንድቢ ቬዲን እና አንድሪያ ቡደኩል ይገኛሉ

Ethiopia Zare (ኀሙስ የካቲት 11 ቀን 2002 ዓ.ም. February 19, 2010)፦ ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ የታሰሩበትን አንደኛ ዓመት በማሰብ፣ እሳቸው እና ሌሎች የኅሊና እስረኞች እንዲፈቱ የሚጠይቅ ታላቅ ህዝባዊ ስብሰባ የፊታችን ቅዳሜ ፌብሩዋሪ 20 ቀን 2010 እ.ኤ.አ. በስቶክሆልም ከተማ ስቬያቬገን 47 በሚገኘው ኤ.ቢ.ኤፍ. ሁሰት አዳራሸ እንደሚደረግ ታወቀ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሮቤል ተክለማሪያም ውድድሩን አካሄደ

Robel Tekelemariam, Vancouver 2010የቶርኒዶ ሰዓቱን አሻሽሏል

Ethiopia Zare (ማክሰኞ የካቲት 9 ቀን 2002 ዓ.ም. February 16, 2010)፦ በቫንኩቨሩ ዊንተር ኦኦሎምፒክ በአገር አቋራጭ የበረዶ ላይ መንሸራተት (ስኪ) ውድድር የተሳተፈው ብቸኛ ኢትዮጵያዊ ሮቤል ተክለማሪያም ትላንት Feb.15/2010 በተደረገው ውድድር ተሳትፎ ከአራት አመት በፊት በቶርኒዶ ኢጣሊያ ያስመዘገበውን ሰዓት አሻሽሎ ውድድሩን ማጠናቀቁ ታወቀ።

ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ዜና ማርቆስ አረፉ

His Eminence Archbishop Abune Zena MarkosEthiopia Zare (እሁድ የካቲት 7 ቀን 2002 ዓ.ም. February 14, 2010)፦ በሲያትሉ ቅዱስ ገብርኤል መቀመጫቸውን አድርገው በተለያዩ ሀገራት ለሚገኙ የኦርቶዶክስ ተዋኅዶ ምዕመናንን ሲያገለግሉ የነበሩት ታላቅ አባት ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ዜና ማርቆስ ትናንት ቅዳሜ የካቲት 6 ቀን 2002 ዓ.ም. አረፉ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሮቤል አቀባበል ተደረገለት

በአውሮፕላን ማረፊየያ ለሮቤል አቀባበል ሲደረግለትEthiopia Zare (ሐሙስ የካቲት 4 ቀን 2002 ዓ.ም. February 11, 2010)፦ በቫንኩቨርሩ የክረምት (ዊንተር) ኦሎምፒክ በበረዶ ላይ መንሸራተት (ስኪ) ውድድር ለመሳተፍ ዝግጅቱን ያጠናቀቀው ወጣት ሮቤል ተክለማርያም፤ ትላንት ከምሽቱ 8፡30 አካባቢ በቫንኩቨር አውሮፕላን ማረፊያ ደማቅ አቀባበል ተደረገለት። ሙሉውን አስነብበኝ ...

ቫንኩቨር ሮቤልን ለመቀበል በዝግጅት ላይ ነች

በሲያትል ኮንሰርቱን የሚያቀርበው ቴዲ አፍሮ ሮቤልን ቀበላል ተብሎ ይጠበቃል

Ethiopia Zare (ቅዳሜ ጥር 29 ቀን 2002 ዓ.ም. February 6, 2010)፦ ለመጀመሪያ ጊዜ ኢትዮጵያን በመወከል ለፈረንጆቹ የክረምት የበረዶ ላይ የስፖርት ውድድር ተሳታፊ የሆነው ሮቤል ተክለማሪያምን ለመቀበል ዝግጅቱ መጠናቀቁን በቨንኮቨር የሚገኘው ግብር ሀይል ለኢትዮጵያ ዛሬ ገለጸ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢትዮጵያዊው ሮቤል በቫንኩቨሩ የክረምት ኦሎምፒክ ይሳተፋል

Robel TeklemariamEthiopia Zare (ሐሙስ ጥር 20 ቀን 2002 ዓ.ም. January 28, 2010)፦ በክረምት ኦሎምፒክ ታሪክ ኢትዮጵያን ወክሎ በመወዳደር የመጀመሪያው የሆነው የ35 ዓመቱ ወጣት ሮቤል ተክለማርያም በሚቀጥለው ወር በቫንኩቨር - ካናዳ በሚጀመረው የክረምት (ዊንተር) ኦሎምፒክ ለመሳተፍ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ገለጸ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአየር መንገዱ አደጋ አጠያያቂ ሆኗል

ጥቁር ሳጥኑ ተገኘ

የሠራተኞች ስም ዝርዝር ይዘናል

Ethiopia Zare (ሐሙስ ጥር 20 ቀን 2002 ዓ.ም. January 28, 2010)፦ በኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራ ቁጥር ET-409 በተከሰተው አሰቃቂ አደጋ ከሞቱት 90 ሰዎች መካከል የ36ቱ አስከሬን የተገኘ ሲሆን፤ በበረራ ሥራ ላይ የተሰማሩት የአየር መንገዱ ሠራተኞች ማንነት መታወቁን የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች ገለጹ። ሙሉውን አስነብበኝ ...