ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ የታሰሩበትን አንደኛ ዓመት የሚያስብ ዝግጅት ተጀምሯል

የፖለቲካ እስረኞች ወር
መታሰቢያው ለአንድ ወር የሚዘልቁ ዝግጅቶችን ያካትታል

የ37 ዓመቷ የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ሊቀመንበር ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ አለአግባብ ከመንገድ ታፍነው ተወስደው የታሰሩበትን አንደኛ አመት የሚያስብና እሳቸውንና ሌሎች በፖለቲካ እምነታቸው ምክንያት የታሰሩ ኢትዮጵያዊያንን ለማስፈታትና ጫና ለማሳደር የሚደረግ ለአንድ ወር የሚቆይ ዝግጅት እየተዘጋጀ መሆኑን የ “ነጻነት ለብርቱካንና ለሁሉም የህሊና እስረኞች” የተሰኘው ግብረሀይል እና ሌሎች የሰብአዊ መብት ድርጅቶች ጊዜያዊ አስተባባሪ ኮሚቴ አስታውቋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ እና አቶ ስየ አብርሃ አንድነት ፓርቲን ለመቀላቀል ወሰኑ

Ato Seye AbrhaDr. Negasso Gidadaጥያቄአቸው የፊታችን እሁድ በአንድነት ፓርቲ ጠቅላላ ጉባዔ ተቀባይነት ያገኛል ተብሎ ይታመናል

ዶ/ር ነጋሶ የኢትዮጵያን ህዝብ ይቅርታ ጠየቁ

Ethiopia Zare (ኀሙስ ኅዳር 17 ቀን 2002 ዓ.ም. November 26, 2009)፦ የቀድሞው የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት የነበሩት ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ እና የህወሓት ታጋይና የቀድሞው የመከላከያ ሚኒስትር የነበሩት አቶ ስየ አብርሃ ዛሬ ኀሙስ ኅዳር 17 ቀን 2002 ዓ.ም. ጠዋት በግዮን ሆቴል በጋራ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ (አንድነት) ፓርቲን ለመቀላቀል መወሰናቸውን ገለጹ። የአባልነት ጥያቄአቸው የፊታችን እሁድ ኅዳር 20 በአንድነት ጠቅላላ ጉባዔ ይፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የታላቁ ሩጫ ተሳታፊዎች ወ/ት ብርቱካን እንድፈታ ጠየቁ፣ ተቃውሟቸውን ገለጹ

ኢንጂ. ኃይሉ ሻውል፣ አቶ ልደቱ አያሌው፣ አቶ አየለ ጫሚሶ፣ ፍትህ ሚኒስቴር፣ … ተወገዙ

9th Great Run 9ኛው ታላቁ ሩጫ

Ethiopia Zare (እሁድ ኅዳር 13 ቀን 2002 ዓ.ም. November 22, 2009)፦ በአትሌት ኃይሌ ገብረሥላሴ አዘጋጅነት በየዓመቱ የሚደረገው ዘጠነኛው ታላቁ ሩጫ በዛሬው ዕለት (ኅዳር 13 ቀን 2002 ዓ.ም.) 33 ሺህ ተሳታፊዎች በተካፈሉበት የተካሄደ ሲሆን፣ ተሳታፊዎቹ የአንድነት ፓርቲ መሪ ወ/ት ብርትኳን ሚደቅሳ እንድትፈታ በጩኸት ጠይቀዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ድምፃዊት ማንአልሞሽ ዲቦ (ዓሣ በለው) አረፈች

Artist Manalmosh Dibo ድምፃዊት ማንአልሞሽ ዲቦ ሼኽ አል-አሙዲ ለሕክምና ወደ ደቡብ አፍሪካ ልከዋት ነበር

Ethiopia Zare (ቅዳሜ ኅዳር 12 ቀን 2002 ዓ.ም. November 21, 2009)፦ “ዓሣ በለው” በሚለው ዘፈኗ በብዙዎች ዘንድ ታዋቂ የሆነችው ድምፃዊት ማንአልሞሽ ዲቦ ዛሬ ማምሻውን (ቅዳሜ ኅዳር 12 ቀን 2002 ዓ.ም.) ለሕክምና ደቡብ አፍሪካ እንደደረሰች ማረፏን የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች ገለፁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሩብ ያህሉ የኢትዮጵያ መሬት ለውጭ ዜጎች ሊሸጥ ነው

የሕንድና የሳውዲ ባለሀብቶች ኢትዮጵያ ናቸው

Ethiopia Zare (አርብ ኅዳር 4 ቀን 2002 ዓ.ም. November 13, 2009)፦ በኢትዮጵያ ለእርሻ አገልግሎት ከሚውለው 14 ሚሊዮን ሔክታር መሬት ውስጥ ከሦስት ሚሊዮን በላይ የሚሆነው ለውጭ ባለሀብቶች እንደሚሸጥ የግብርና ኢንቨስትመንት ኤጀንሲ አስታውቋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...