ማይክል ጃክሰን በ50 ዓመቱ አረፈ

ማይክል ጃክሰን Michael Jackson (Photo: AFP) 

Ethiopia Zare (ዓርብ ሰኔ 19 ቀን 2001 ዓ.ም. June 26, 2009)፦ ይህ ዜና ከመፃፉ ከ7 ደቂቃ በፊት የፖፕ ሙዚቃው ንጉሥ ማይክል ጃክሰን በ50 ዓመቱ ኀሙስ ሰኔ 18 ቀን 2001 ዓ.ም. (June 25, 2009) ማረፉን አሶሺየትድ ፕሬስ ዘገበ። እንደ ዘገባው ከሆነ ለጉዳዩ ቅርበት ያለው ስሙ በይፋ እንዳይገለጽ የፈለገና በኦፊሴል የማይክልን ሕልፈተ ሕይወት ለመግለጽ ያልተፈቀደለት ግለሰብ፤ ማይክል ጃክሰን በሎስ አንጀለስ ሆስፒታል ውስጥ ማረፉን አረጋግጧል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አንድነት መድረክ ጋር የሚያሠሩ ነጥቦች ላይ ውሳኔ ይሰጣል

Ethiopia Zare (ኀሙስ ሰኔ 18 ቀን 2001 ዓ.ም. June 25, 2009)፦ አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ከመድረክ ለምክክር ጋር በጋራ ሊያሠሩ ይችላሉ ተብለው በታመኑባቸው ነጥቦች ላይ በቅርቡ ውሳኔ እንደሚሰጥ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊው ዶ/ር ኃይሉ አርኣያ በተለይ ለኢትዮጵያ ዛሬ ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የግልገል ግቤ 3 ግድብ ውዝግብ እንደቀጠለ ነው

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ሰኔ 16 ቀን 2001 ዓ.ም. June 23, 2009)፦ በአራት የተለያዩ አካላት አጨቃጫቂ እየሆነ በመጣው የግልገል ግቤን የኃይድሮኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ላይ “አሉባልታዎችና ውዥንብሮችን የሚነዛ በህዝብና በሀገር ጥቅም ላይ የተነሳ ነው” ሲል የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት አሳወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሱዳንና ኢትዮጵያ ወታደራዊ ስምምነት አደረጉ

ግብጽ ደስተኛ አይደለችም

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ሰኔ 16 ቀን 2001 ዓ.ም. June 23, 2009)፦ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ወዳጅነታቸው እየጠነከረ የመጣው ኢትዮጵያ እና ሱዳን በወታደራዊ ሥልጠና ዙሪያ ለሦስት ዓመታት የሚቆይ ወታደራዊ ስምምነት በመከላከያ ሚኒስትሮቻቸው በኩል ተፈራረሙ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በያዝነው ዓመት 12 የጐሣ ግጭት መከሰቱን ፖሊስ አመነ

Ethiopia Zare (ዓርብ ሰኔ 5 ቀን 2001 ዓ.ም. June 12, 2009)ሀገሪቱን ብሔር ብሔረሰቦች ሸንሽኖ በሚገዛው በኢህአዴግ መንግሥት አስተዳደር ውስጥ 10 ወራት ብቻ 12 ብሔር ብሔረሰቦችና የጐሳ ግጭቶች በኢትዮጵያ ተከስቶ እንደነበር የፌዴራል ፖሊስ ዋና ዳይሬክተር አቶ ወርቅነህ ገበየሁ አሳወቁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ፕሮፌሠሩ በህወሓት ሰዎች ተተቹ

Ethiopia Zare (ዓርብ ሰኔ 5 ቀን 2001 ዓ.ም. June 12, 2009)፦ በአሜሪካን ሀገር “The Ethiopian Revolution war in the Horn of Africa” በሚል ርዕስ መጽሐፍ ጽፈው ያሰራጩት ፕሮፌሠር ገብሩ ታረቀ ባለፈው ሣምንት በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የኢህአዲግ ባለሥልጣናትና ጄኔራሎች በተገኙበት ስብሰባ በህወሓት ሰዎች ትችት ቀረበባቸው። ሙሉውን አስነብበኝ ...

በእስር ቤት ልጅ መውለድ ምን እንደሚመስል ጋዜጠኛ ሰርካለም ፋሲል ገለጸች

በኖርዌዩ የውይይት መድረክ ላይ እንዳትሳተፍ ኢህአዲግ ከሀገር እንዳትወጣ ከለከላት

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ሰኔ 2 ቀን 2001 ዓ.ም. June 9, 2009)፦ ከጁን አንድ እስከ ስድስት 2009 እ.ኤ.አ. በኖርዌይ ዋና ከተማ ኦስሎ በተደረገው ሦስተኛው ”ዓለም አቀፍ የሃሳብ ነፃነት የውይይት መድረክ” (Global Forum on Freedom of Expression) ላይ ልዩ ቦታ ተሰጥቷት ዋና ተናጋሪ በመሆን ተጋባዥ የነበረችው ጋዜጠኛ ሰርካለም ፋሲል፤ ከኢትዮጵያ እንዳትወጣ የኢህአዲግ መንግሥት ስለከለከላት በውይይት መድረኩ ላይ ለመገኘት አልቻለችም። በውይይቱ ላይ በጽሑፍ የላከችው ንግግር መልዕክት ለታዳሚዎቹ ተነብቧል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ወ/ት ብርቱካን ቅዳሜ እንድትጎበኝ ተፈቅዶ በማግስቱ እሁድ ተከለከለ

አንድነት አዳራሽ ለመሥራት ከ4 - 7 ሺህ ዶላር ያስፈልገዋል ተባለ

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ሰኔ 2 ቀን 2001 ዓ.ም. June 9, 2009)፦ የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ሊቀመንበር ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ ከአምስት ወራት የእስር ጊዜ በኋላ ቅዳሜ ዕለት ከተመደቡላት የዘወትር ጠያቂዎቿ በተጨማሪ ሌሎች ሰዎች የጎበኟት ሲሆን፤ በተቃራኒው እሁድ ዕለት በድጋሚ ከዘወትር ጠያቂዎቿ ውጭ ማንንም ሰው ማስገባት አይቻልም ተብሎ፤ በተለይ የድርጅቱ ከፍተኛ አመራር አባላቶች እስከመግፋት በደረሰ ማመናጨቅ እንዳባረሩዋቸው ለማወቅ ተችሏል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...