አንጋፋው አርቲስት ዓለሙ ገብረአብ አረፈ

 አርቲስት ዓለሙ ገብረአብ Alemu Gebreabዛሬ አርብ ሥርዓተ ቀብሩ ተፈጸመ

Ethiopia Zare (አርብ ሐምሌ 3 ቀን 2001 ዓ.ም. July 10, 2009)፦ አንጋፋው ከዚህ አለም በሞት መለየቱንና ዛሬ ዕለተ አርብ ሐምሌ 3 ቀን 2001 ዓ.ም. ከቀኑ 6 ሰዓት ከ30 በየካ ሚካኤል ቤተ-ክርስቲያን መካነ-መቃብር ሥርዓት ቀብሩ መፈጸሙን የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች አረጋገጡ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አቶ በረከት በፕላዝማ ለመምህራን አብዬታዊ ዲሞክራሲን ሰበኩ

መምህራን ፍላጐታቸው የትምህርት ጥራትና ኑሮን ያገናዘበ ደሞዝ ማግኘት መሆኑን አሳወቁ

Ethiopia Zare (ቅዳሜ ሰኔ 27 ቀን 2001 ዓ.ም. July 4, 2009)፦ ሰኔ 21 ቀን ከጠዋቱ 2 ሰዓት ተኩል በኋላ መምህራን ወደ አጋርፋና ፍቼ እንደዚሁም ሌሎች አካባቢዎች ለፖለቲካዊ ንቃት ከተንቀሳቀሱ ወዲህ ሰኞ ሰኔ 22 ቀን 2001 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማም ጭምር የተጀመረው የአብዮታዊ ዴሞክራሲ፣ የልማታዊ መንግስት እና የፍትሃዊ ሥርዓት ትምህርት በዛሬውም እለት ቀጥሎ ውሏል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ከአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ ከ500 የሚበልጡት እንደሚባረሩ ተገለጸ

Ethiopia Zare (ቅዳሜ ሰኔ 27 ቀን 2001 ዓ.ም. July 4, 2009)፦ በጦላይ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ማዕከል ከተካሄደው 3ኛ ዙር የሥነ-ምግባር ነክ ግምገማ በኋላ፣ ከአዲስ አበባ ከተማ የፖሊስ ሠራዊት ባለደረቦች መካከል ከ500 የሚበልጡት “ይባረራሉ፣ በሂስና በግለ-ሂሱ መድረክ ወንጀል ስለመፈጸማቸው ያመኑትና ምስክር የቆመባቸው ፖሊሶች የክስ ፋይል ይከፈትባቸዋል” ተባለ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የፓትርያርኩና የጳጳሱ ሽኩቻ ተባብሷል

“ቃለ ዓዋዲው ይዳኛችሁ” ጠ/ሚ መለስ

Ethiopia Zare (ቅዳሜ ሰኔ 27 ቀን 2001 ዓ.ም. July 4, 2009)፦ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በፓትርያሪኩና በአቡነ ሳሙኤል መካከል ተከስቶ የነበረው ግጭት መባባሱንና ባለፈው ማክሰኞ ስብሰባ የቤተክህነት ውዝግብ መቀጠሉ ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አትሌት ቀነኒሳ፣ መሰረት እና ደረሰ በኦስሎው ጎልደን ሊግ አሸነፉ

Meseret Defar አትሌት መሰረት ደፋርKenenisa Bekele አትሌት ቀነኒሳ በቀለEthiopia Zare (አርብ ሰኔ 26 ቀን 2001 ዓ.ም. July 3, 2009)፦ በያዝነው የአውሮፓውያን 2009 እየተካሄደ ባለው የኤ.ኤፍ. ጎልደን ሊግ አትሌቲክስ በ5 ሺህ ሜትር ርቀት አትሌት ቀነኒሳ በቀለ እና መሰረት ደፋር በኖርዌይ ዋና ከተማ ኦስሎ ውድድሩን በአንደኝነት አጠናቀቁ። የጎልደን ሊጉን አንድ ሚሊዮን ዶላር ሽልማት ይቋደሳሉ ተብለው ከሚጠበቁት አትሌቶች ውስጥ ሁለቱ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ይገኙበታል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አንድነት በደብረማርቆስ የተሳካ ስብሰባ አካሄደ

“አቶ ስዬ አብርሃ አንድነትን ለመቀላቀል ጥያቄ አላቀረቡም፤ ማመልከቻም አላስገቡም” ዶ/ር ኃይሉ አርኣያ

Ethiopia Zare (አርብ ሰኔ 26 ቀን 2001 ዓ.ም. July 3, 2009)፦ አንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ ባለፈው እሁድ በደብረ ማርቆስ ከተማ ያካሄደው ስብሰባ ብዙ ፈተናዎች ቢያጋጥሙትም በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁ ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በደሴ የሟቾች ቁጥር አራት ደርሷል፤ የቁስለኞችም ቁጥር አሻቅቧል

አባ ጳውሎስ ከ“ሕገ-ወጦች ጋር” አናብርም አሉ

Ethiopia Zare (ረቡዕ ሰኔ 24 ቀን 2001 ዓ.ም. July 1, 2009)፦ በደሴ ከተማ ፌደራል ፖሊሶች በክርስትና እምነት ተከታዮች ላይ በወሰዱት የጭካኔ እርምጃ ምክንያት የሞቱ ሰዎች ቁጥር ከሁለት ወደ አራት ከፍ ብሏል። ከስፍራው በተቃውሞ ሰልፉ የተሳተፈች ሴትና የፖሊስ ዱላ ያረፈባት ሴት እንደገለጸችልን ከሆነ አንዱ ሟች ከላሊበላ የመጣ በስንቅ የሕክምና ትምህርት የሚከታተል ወጣት ሲሆን፤ አስከሬኑ ወደቤተሰቦቹ መሄዱን ገልጻለች።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በደሴ ከተማ ምዕመናንና ፖሊስ ተፋጠዋል፤ መሣሪያ ሲተኮስ ውሎ አንድ መነኩሴ ሞተዋል

ገዢው ፓርቲ ክርስቲያኑንና ሙስሊሙን ማናከሱን ገፍቶበታል

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ሰኔ 23 ቀን 2001 ዓ.ም. June 30, 2009)፦ በደሴ ከተማ የቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን እንድትሠራበት ታቅዶበት የነበረው ቦታ ለረዥም ጊዜ ሲያወዛግብ ቆይቶ፤ የከተማው አስተዳደር ባለሥልጣናት ቦታውን ሙስሊሞች ተቃውመውታል በሚል ሥራው ተቋርጦ በድንኳን ሲቀደስበት ከቆየ በኋላ፤ መንግሥት መልሶ ቦታውን ለሌላ አገልግሎት ይዠዋለሁ በማለቱ ዛሬ በደሴ ከተማ ብዛት ያለው ህዝብ የተሳተፈበት ሠላማዊ ሰልፍ እንደተካሄደና ከሰልፉ በኋላ በምዕመናንና በፌደራል ፖሊሶች መካከል ረብሻ መነሳቱን የዓይን ምስክሮች ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አቶ አበበ ወርቄ በፖሊስ ተይዘው አልቀረቡም

ለሕክምና ወደ ውጭ ሄደዋል ተባለ

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ሰኔ 23 ቀን 2001 ዓ.ም. June 30, 2009)፦ ከአዲስ ብሮድካስቲንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ያለቀረጥ የገቡ የሕትመት መሣሪያዎችን አላግባብ መጠቀም በሚል ክስ ተጠርጥረው ታስረው በዋስ የተለቀቁት እውቁ የሕግ ባለሙያ አቶ አበበ ወርቄ በፖሊስ ተይዘው እንዲቀርቡ ትዕዛዝ ቢወጣባቸውም፤ ዛሬ በዋለው የፍርድ ቤት ውሎ በሕመም ምክንያት ወደ ውጭ ሀገር በመሄዳቸው ሊቀርቡ አለመቻላቸውን የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...