ወ/ት ብርቱካን የምትፈታበት ተስፋ እንዳለ የሀገር ሽማግሌዎቹ ገለጹ

Prof. Ephraim Issac ፕ/ር ኤፍሬም ይስኃቅ Ethiopia Zare (አርብ ሚያዝያ 23 ቀን 2001 ዓ.ም. May 1, 2009)፦ የሚመራው የሀገር ሽማግሌዎች ቡድን ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ በታሰረች በአራት ወር ከአራት ቀናቸው ዛሬ ማምሻውን ከ10፡10 ሰዓት በኋላ በአዲስ አበባ በሸራተን ሆቴል ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጠ። በመግለጫቸው ላይ የሽምግልና ዝርዝር ሂደቱን ለመግለጽ ፈቃደኞች ያልነበሩ ሲሆን፤ ወ/ት ብርቱካን የምትፈታበት ተስፋ እንዳለ ገልጸዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የቫንኩቨር ቅ/ማርያም ክርክር ተጠናቀቀ

የዳኛ ውሳኔ ይጠበቃል

Ethiopia Zare (አርብ ሚያዝያ 23 ቀን 2001 ዓ.ም. May 1, 2009)፦ ከሁለት ዓመት በላይ የወሰደው የቫንኩቨር ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተክርስቲያን ውዝግብ በተለያየ ጊዜ በተደረጉና ሦስት ሣምንታትን በወሰደው ችሎት ትላንት ጠበቆች ባቀረቡት የማጠቃለያ ሃሳብ መጠናቀቁ ታወቀ። ዳኛው ውሳኔያቸውን እስኪሰጡ ከሳሽና ተከሳሽ ወገኖች በትዕግስት እንዲጠበቁ ጠይቀዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

“የግንቦት 7 ዓላማ መፈንቅለ መንግሥት ማካሄድ ሳይሆን ባለሥልጣኖችን መግደል ነበር” አቶ በረከት ስምዖን

Ato Bereket Semeon, አቶ በረከት ስምዖንEthiopia Zare (አርብ ሚያዝያ 23 ቀን 2001 ዓ.ም. May 1, 2009)፦ “የግንቦት 7 ንቅናቄ ዓላማ መፈንቅለ መንግሥት ማካሄድ ሳይሆን ባለሥልጣናቶችን መግደል ነበር” ሲሉ የመንግሥት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ በረከት ስምዖን በዛሬው ዕለት ለጋዜጠኞች መግለጫ ሰጡ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አቶ ታምራት ታረቀኝ ከአንድነት ፓርቲ ታገዱ

Ethiopia Zare (አርብ ሚያዝያ 23 ቀን 2001 ዓ.ም. May 1, 2009)፦ በኢትዮጵያ የተቃውሞ ፖለቲካ ታሪክ ከ1987 ዓ.ም. ጀምሮ ጉልህ ስፍራ ያላቸውና፣ ከቅንጅት አመራሮች ጋር ለ21 ወራት ታስረው የተፈቱት የአሁኑ የአንድነት ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ አባልና የወጣቶች ጉዳይ ኃላፊ አቶ ታምራት ታረቀኝ በብዕር ስም በጋዜጣ ጽፈው ባወጡት ጽሑፍ ፖርቲውን አደጋ ላይ ጥለዋል በሚል ዛሬ ጠዋት ከአንድነት ፓርቲ ለአንድ ወር ታገዱ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ፕሮፌሠር ኤፍሬም ከወ/ት ብርቱካን እስር በኋላ የመጀመሪያውን መግለጫ በጽሑፍ ሰጡ

Prof. Ephraim Issac ፕ/ር ኤፍሬም ይስኃቅመግለጫው ስለይቅርታው ሂደት ዝርዝር የለውም

Ethiopia Zare (አርብ ሚያዝያ 23 ቀን 2001 ዓ.ም. May 1, 2009)፦ ከወ/ት ብርቱካን መታሰር በኋላ ድምፁን አጥፍቶ የነበረው የሀገር ሽማግሌዎች ሕብረት መሪ ፕሮፌሠር ኤፍሬም ይስኃቅ ኢትዮጵያ በመሆናቸው በዛሬው ዕለት በ10 ሰዓት በሸራተን ሆቴል መግለጫ እንደሚሰጡ ለጋዜጠኞች ጥሪ ያስተላለፉ ሲሆን፣ በሌላ በኩል የቅንጅት አመራሮች የተፈቱበትን የይቅርታ ሂደት በሚገባ የማያብራራ መግለጫ ትናንት ኀሙስ ሚያዝያ 22 ቀን 2001 ዓ.ም. ለተወሰኑ ጋዜጠኞች በጽሑፍ ሰጥተዋል። የመግለጫው ሙሉ ቃል እንደሚከተለው አቅርበነዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአንድነት ብሔራዊ ምክር ቤት አባል በግንቦት ሰባት ስም ተጠርጥው ከታሰሩት ውስጥ አንዱ ናቸው

የዶ/ር ብርሃኑ ነጋ የቅርብ ዘመድ ከአቶ ነጋ ቦንገር ቤት ተይዘው ታስረዋል

Ethiopia Zare (አርብ ሚያዝያ 23 ቀን 2001 ዓ.ም. May 1, 2009)፦ ባለፈው ሣምንት የብሔራዊ መረጃ ደህንነት አገልግሎትና የፌደራል ፖሊስ የጋራ ፀረ-ሽብር ግብረ ኃይል ባወጣው መግለጫ ከግንቦት 7 ጋር በተያያዘ ተጠርጣሪ ናቸው ብሎ ካሰራቸው 35 ሰዎች ውስጥ፤ የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ መስራችና የምክር ቤት አባል አቶ መላኩ ተፈራ፣ በኢህአዴግ የትጥቅ ትግል ዘመን ስመጥር የጦር መሪ ብርጋዴር ጄኔራል ተረፈ ማሞ፣ የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ አባት የ80 ዓመቱ አቶ ጽጌ ኃብተማርያም እና የዶ/ር ብርሃኑ ነጋ የቅርብ ዘመድ አቶ ጌቱ ወርቁ ይገኙበታል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የስዊድን የአንድነት ድጋፍ ማኅበር ለዶ/ር ጥላሁን ገሠሠ የመታሰቢያ ዝግጅት አደረገ

በወዛደሮች ቀን ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ እንድትፈታ በኢትዮጵያውያን ሰልፍ ይደረጋል

By Matias Ketema (Sweden)

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ሚያዝያ 20 ቀን 2001 ዓ.ም. April 28, 2009)፦ የስዊድን የአንድነት ፓርቲ ድጋፍ ማኅበር ቅዳሜ ሚያዝያ 17 ቀን 2001 ዓ.ም. (አፕሪል 25 ቀን 2009) ቀን ዶ/ር ጥላሁን ገሠሠን በማሰብ ዝግጅት አደረገ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

ወ/ት ብርቱካን በወዳጅ ዘመድ እንድትጎበኝ ፍርድ ቤት ቢያዝም ማረሚያ ቤቱ ፍቃደኛ አልሆነም

ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳአንድ ዘመዷና ሹፌሯ ብቻ ተፈቅዶላቸዋል

Ethiopia Zare (ቅዳሜ ሚያዝያ 17 ቀን 2001 ዓ.ም. April 25, 2009)፦ ለሦስት ወራት ከ17 ቀን ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ በታጣቂዎች ታፍና ወደ ቃሊቲ እስር ቤት የተጣለችው ብቸኛዋ የሴት የፖለቲካ መሪ ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ በጠበቃዋ፣ በሐኪሟ፣ በኃይማኖት አባቷ፣ በቤተሰቦቿ፣ በወዳጅ ዘመዶቿና በጓደኞቿ የመጎብኘት መብቷ የተረጋገጠ ቢሆንም የምትገኝበት ቃሊቲ የሚገኘው የአዲስ አበባ ማረሚያ ቤት ዛሬም ጠያቂዎቿን ማስገባት ከለከለ። የአክስቷ ልጅ እና ሹፌሯ ብቻ ተፈቅዶላቸዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...