የአራት ከፍተኛ የጦር መኮንኖች የወንጀል ምርመራ ተቋረጠ

Ethiopian Federal Police Commission Crime Investigation Bureau (EFPCCIB)

ከእስር የተለቀቁት የወንጀል ተሳትፎአቸው ዝቅተኛ በመኾኑ ነው

ኢዛ (ረቡዕ የካቲት ፲ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. February 17, 2021)፦ በሰሜን ዕዝ ላይ በተሰነዘረው ጥቃት ላይ ተሳትፈዋል ተብለውና በተለያዩ ወንጀሎች ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር የሚገኙ አራት ከፍተኛ የጦር መኮንኖች ላይ ሲያካሒድ የነበረው የወንጀል ምርመራ ማቋረጡን የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ወንጀል ምርመራ ቢሮ አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአሜሪካው ኩባንያ የንግድ ባንክን አዲስ አደረጃጀት ለማዘጋጀት የወጣውን ጨረታ አሸነፈ

Commercial Bank of Ethiopia (CBE) and McKinsey & Company

ባንኩ በስድስት ወር ውስጥ ከ7.4 ቢሊዮን በር በላይ አትርፏል

ኢዛ (ረቡዕ የካቲት ፲ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. February 17, 2021)፦ ማኬንዚ የተባለው የአሜሪካ ኩባንያ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን አጠቃላይ አደረጃጀት ለመቀየር የሚያስችለውን ጥናትና አዲስ መዋቅር ለማዘጋጀት የወጣውን ዓለም አቀፍ ጨረታ ማሸነፉ ተገለጸ። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በስድስት ወር ውስጥ ከ7.4 ቢሊዮን ብር በላይ አተረፍኩ አለ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በሕገወጥ መንገድ የተከማቸው ሁለት ሚሊዮን ጄሪካን ዘይት ለሸማቾች እየተሰራጨ ነው

Palm Oil

ሸሽጎ ያስቀመጠው ማን እንደኾነ እስካኹን አልተገለጸም

ኢዛ (ሰኞ የካቲት ፰ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. February 15, 2021)፦ በአዲስ አበባ በአንድ ግለሰብ መጋዘን ውስጥ በሕገወጥ መንገድ ተከማችቶ የተገኘው ሁለት ሚሊዮን ጄሪካን ፓልም የምግብ ዘይት፤ ሸሽጎ ያስቀመጠው ማን እንደኾነ ሳይታወቅ ለሸማች ማኅበራት እየተሰራጨ መኾኑ ተገጸለ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወለጋ

PM Abiy Ahmed

ወለጋ ለኢትዮጵያ ነፃነት ሕልውና ተምሳሌት መኾኑን ገለጹ

ኢዛ (ሰኞ የካቲት ፰ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. February 15, 2021)፦ “ወለጋ የኦሮሞ ሕዝብና ለኢትዮጵያ ነፃነትህ ሕልውና ተምሳሌት ነው” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኦነግ በምርጫው መሳተፍ አለመሳተፉ አልለየም

Kejela Merdasa (OLF)

የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊው የመሳተፋችን ነገር 50 በመቶ ነው ይላሉ

ኢዛ (ሰኞ የካቲት ፰ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. February 15, 2021)፦ በኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) አመራር አባላት መካከል ያለውን አለመግባባት ለመፍታት የተለያዩ ማጣራቶች ሲያደርጉ መቆየቱ የሚታወስ ቢኾንም፤ ግንባሩ በቀጣዩ ምርጫ (ምርጫ 2013) የመሳተፍ እድል 50 በመቶ መኾኑን የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊው ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኢዜማ የአንድ የምርጫ ወረዳ ሊቀመንበሩ ተገደሉ

Girma Moges Legesse

በተተኮሰባቸው ጥይት ሕይወታቸው ማለፉን ፓርቲው አስታውቋል

ኢዛ (ሰኞ የካቲት ፰ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. February 15, 2021)፦ በቀጣዩ አገራዊ ምርጫ (ምርጫ 2013) በዋናነት ተፎካካሪ እንደሚኾኑ ከሚጠበቁት ተፎካካሪ ፓርቲዎች መካከል አንዱ የኾነው የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) በደብረዘይት (ቢሾፍቱ) ከተማ የአድአ ምርጫ ወረዳ 1 ሊቀመንበሩ እንደተገደለበት አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሱዳን ትንኮሳ ብሷል

Ethio-Sudan border

ድንበር ጥሳ በያዘችው መሬት ላይ ግንባታዎች ማካሔድ ጀምራለች

ኢዛ (ሰኞ የካቲት ፰ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. February 15, 2021)፦ የኢትዮጵያ መንግሥት በትግራይ ያካሔደውን የሕግ ማስከበር ዘመቻ ማጠናቀቁን ካስታወቀ በኋላ፤ ሱዳን የኢትዮጵያን ድንበር ጥሳ በመግባት የያዘችውን መሬት ከመልቀቅ ይልቅ፤ በቦታው ላይ ይዞታዋን የማጠናከር ተግባር ስለመቀጠልዋ እየተነገረ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሕገወጥ ተግባር ጥግ በኢትዮጵያ

ፓልም የምግብ ዘይት

በየደረጃው በመንግሥት አካል ውስጥ ያሉ ባለሥልጣናት ተባባሪ የኾኑበት ተግባር ነው የሚል ግምት አሳድራል

ኢዛ (ሰኞ የካቲት ፰ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. February 15, 2021)፦ በኢትዮጵያ ሕገወጥ ተግባራት ምን ያህል ደረጃ ላይ እንደደረሱ በርካታ ማሳያዎች በየዕለቱ እየወጡ ነው። የመሬት ዘረፋና ወረራ አንዱ ሲሆን፤ ሌሎችም አንዳንዴ ሊገመቱ የማይችሉ ሕገወጥ ተግባራት በተከታታይ እየተሰሙ ነው። ቅዳሜ ዕለት የተሰማው አንዱ ዜና ደግሞ በአገሪቱ ውስጥ የተፈጸሙ እና እየተፈጸሙ ያሉ ሕገወጥ ተግባራት በየዘርፉ መኖራቸውን ያሳያል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢትዮጵያ በ12 ዓመት ለነዳጅ ግዥ ከግማሽ ትሪሊዮን ብር በላይ ወጪ አድርጋለች

Petroleum

አገሪቱ ከምታገኘው የውጭ ምንዛሪ ገቢ ላይ ግማሹ ለነዳጅ ግዥ ይውላል

ኢዛ (እሁድ የካቲት ፯ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. February 14, 2021)፦ የኢትዮጵያ መንግሥት ከፍተኛ ወጪ ከሚያወጣባቸው ምርቶች መካከል አንዱ ለኾነው ለነዳጅ ግዥ ባለፉት 12 ዓመታት ከግማሽ ትሪሊዮን ብር በላይ ብር ወጪ አውጥቷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ