ጠቅላይ ሚኒስትሩ በምርጫው ከተወዳደሩ ፓርቲ መሪዎች ጋር መከሩ

PM Abiy Ahmed

እናመሰግናችኋለን ብለዋቸዋል

ኢዛ (ሰኞ ሰኔ ፳፩ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. June 28, 2021)፦ ስድስተኛው አገራዊ ምርጫ 2013 በተደረገ በአንደኛ ሳምንቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ በምርጫው ከተወዳደሩ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎች ጋር መምከራቸውና ምስጋና ማቅረባቸው ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ማዕድን ቡናን ሊበልጥ?

Takele Uma, Minister for Mines, Petroleum and Natural Gas of Ethiopia

በቀጣዩ ዓመት ከማዕድን ዘርፍ 1.5 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሪ ለማግኘት ታቅዷል
የጸጥታ ችግር እንዲፈታ ተጠይቋል

ኢዛ (እሁድ ሰኔ ፳ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. June 27, 2021)፦ ኢትዮጵያ ከማዕድን ዘርፍ የምታገኘው የውጭ ምንዛሪ ባለፉት ሁለት ዓመታት መሻሻል የታየበት ሲሆን፣ በሚቀጥለው በጀት ዓመትም ከ1.5 (ከአንድ ነጥብ አምስት) ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ለማግኘት እቅድ መያዙንና ባለፉት 11 ወራትም ከ668 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱ ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሰብአዊ መብት ኮምሽን በምርጫው ዙሪያ የመጀመሪያውን ሪፖርት ይፋ አደረገ

Ethiopian Human Rights Commission

በተፎካካሪ ፓርቲ አባላቶች እና ደጋፊዎች ላይ ግድያ፣ ድብደባ እና የአካል ጉዳት ደርሷል

ኢዛ (ቅዳሜ ሰኔ ፲፱ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. June 26, 2021)፦ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮምሽን በስድስተኛው አገራዊ ምርጫ 2013 ላይ ኮምሽኑ ያካሔደውን አጠቃላይ ክትትልና ግምገማ፣ እንዲሁም ተፈጸሙ ያላቸውን ግድፈቶች የሚያመላክተውን የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱን ይፋ አደረገ። በተፎካካሪ ፓርቲ አባላቶች እና ደጋፊዎች ላይ ግድያ፣ ድብደባ እና የአካል ጉዳት መድረሱን ሪፖርቱ አካትቷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የጄኔራል ባጫ መግለጫ እያነጋገረ ነው

ጄኔራል ባጫ ደበሌ

በህዳሴው ግድብ ዙሪያ ያለ ችግር በድርድር እንዲፈታ ኢትዮጵያ ያላት ፍላጐት እንደተጠበቀ ነው
በጦርነት እንፈታለን ከተባለም ኢትዮጵያ ዝግጁ ነች
ግድቡ ከተነካ ግብጽና ሱዳንን ጠራርጐ ባሕር ይቀላቅላቸዋል

ኢዛ (ቅዳሜ ሰኔ ፲፱ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. June 26, 2021)፦ በሞስኮ የዓለም አቀፍ የጸጥታ ጉዳዮች ጉባዔ ላይ ተሳታፊ የነበሩት ሌተናል ጄኔራል ባጫ ደበሌ በህዳሴ ግድብ ዙሪያ ኢትዮጵያ ከሱዳን እና ከግብጽ ጋር የተፈጠረውን አለመግባባት በጦርነት ለመፍታት ፍላጐት የሌላት መኾኑን፤ ነገር ግን ኢትዮጵያን ሉዓላዊነቷን ለሚደፍር ጠላት ግን ዝግጁ መኾኗን ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በሽብርተኝነት የተፈረጀው የሕወሓት አባላት ሕንፃዎች በገለልተኛ አካላት እንዲተዳደሩ ተወሰነ

በገለልተኛ አካል እንዲተዳደሩ ከተወሰነባቸው የጥቂቱ የሕወሓት አባላት ሕንጻዎች

ኮሜርሻል ኖሚኒስና የቤቶች ኮርፖሬሽን ሕንፃዎቹን ያስተዳድራሉ
የጀኔራል ፃድቃንና የጀኔራል ታደሰ ሕንፃዎች ይገኙበታል

ኢዛ (ዓርብ ሰኔ ፲፰ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. June 25, 2021)፦ በአሸባሪነት የተፈረጀው የሕወሓት ዋና ዋና አባላት የንግድ እና የመኖሪያ ሕንፃዎች ላይ ገለልተኛ አስተዳዳሪ እንዲሾም ውሳኔ ተላለፈ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢትዮጵያ በህዳሴ ግድብ ዙሪያ ያላትን አቋማ ለጸጥታው ምክር ቤት አስታወቀች

The Grand Ethiopian Renaissance Dam (GERD)

ምክር ቤቱ ድርድሩ ውስጥ ይግባ ብለው ሱዳንና ግብጽ ያቀረቡትን ጥያቄ ውድቅ አደረገች

ኢዛ (ዓርብ ሰኔ ፲፰ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. June 25, 2021)፦ ግብጽ እና ሱዳን በታላቁ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ በአፍሪካ ሕብረት እየተደረገ ያለውን ድርድር እንዲያከብሩ ኢትዮጵያ ለጸጥታው ምክር ቤት ጥያቄ አቀረበች። የግብጽንና የሱዳንን ጥያቄም ውድቅ አደረገች።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሰብአዊ መብት ኮሚሽን ምክትል ዋና ኮሚሽነር ተሰየመለት

Danile Bekele (PHD), Ethiopian Human Rights Commission

የሦስት የዘርፍ ኮሚሽኖችም ሹመት ጸደቀ

ኢዛ (ዓርብ ሰኔ ፲፰ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. June 25, 2021)፦ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽንን (ኢሰመኮን) በምክትል ኮሚሽነርነት እና በተለያዩ ዘርፎች ኮሚሽን ኾነው የሚያገለግሉ ተሿሚዎች ሹመት ዛሬ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጸደቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአንድ የግል ተወዳዳሪ የድምፅ መስጫ ወረቀት ላይ ባለመካተቱ ከ100 በላይ የምርጫ ጣቢያዎች ምርጫ ታገደ

Birtukan Mideksa

በኦሮሚያ ክልል በነገሌ በእነዚህ ምርጫ ጣቢያዎች ምርጫው በድጋሚ ይካሔዳል

ኢዛ (ሐሙስ ሰኔ ፲፯ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. June 24, 2021)፦ በኦሮሚያ ክልል በነገሌ ምርጫ ክልል ከ100 በላይ በሚኾኑ የምርጫ ጣቢያዎች ምርጫው እንዳይካሔድ የተላለፈን መመሪያ በመጣስ በመካሔዱ በእነዚህ ጣቢያዎች የተደረገው ምርጫ 2013 ተቀባይነት እንደማይኖረው የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ገለጸ። ይህ የተፈጠረበት ምክንያት ምርጫ ቦርድ ድምፅ መስጫ ወረቀቱ ላይ በግል የተወዳደሩትን ግለሰብ ባለማሳተሙ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢዜማ በምርጫው ባጋጠሙን ችግሮች ላይ ምርጫ ቦርድ ውሳኔ የማይሰጥ ከኾነ ፍ/ቤት እሔዳለሁ አለ

Ethiopian Citizens for Social Justice

ፓርቲው ነገም ቀጣይ ፓርቲ ኾኖ የሚዘልቅ ስለመኾኑ ገልጿል

ኢዛ (ሐሙስ ሰኔ ፲፯ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. June 24, 2021)፦ ባለፈው ሰኞ ሰኔ 14 ቀን በተካሔድው ምርጫ 2013፣ ኢዜማ በተወዳደረባቸው በርካታ የምርጫ ክልሎች ያጋጠሙትንና ለምርጫ ቦርድ ያሳወቃቸውን በርካታ ተግዳሮቶችን ተመልክቶ ውሳኔ የማይሰጥባቸው ከኾነ ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት እንወስዳለን አለ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢትዮጵያ ባለድርሻ የኾነችበት የበርበራ ወደብ ተርሚናል ሥራ ጀመረ

ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ፣ አቶ አሕመድ ሸዴ፣ ፕሬዝዳንት ሙሳ ቢሂ አብዲ፣ የዲፒ ወርልድ ዳይሬክተር ሱልጣን ቢን ሱለይማን እና አቶ ሙስጠፌ መሐመድ (ከግራ ወደቀኝ)

ኢትዮጵያ 19%፣ ሶማሌላንድ 30% እና ዲፒ ወርልድ 51% ድርሻ አላቸው

ኢዛ (ሐሙስ ሰኔ ፲፯ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. June 24, 2021)፦ በሶማሌላንድ በርበራ ወደብ በኢትዮጵያ አሥራ ዘጠኝ በመቶ የባለቤትነት ድርሻ የተያዘው የበርበራ ተርሚናል ኮሪደርና የመጀመሪያ ዙር ማስፋፊያ ፕሮጀክት ተጠናቆ አገልግሎት ጀመረ። ቀሪው ድርሻ 30 በመቶ የሶማሌላንድ ሲሆን፣ 51 በመቶ ደግሞ የዲፒ ወርልድ እንደኾነ ታውቋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ