የምርጫው ቀን ለሦስት ሳምንታት ሊራዘም እንደሚችል ታወቀ

ምርጫ ቦርድ

በመራጮች ምዝገባ ሒደትና በሌሎች ክንውኖች ላይ በተፈጠረው መዘግየት ምክንያት መኾኑ ተገልጿል

ኢዛ (ቅዳሜ ግንቦት ፯ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. May 15, 2021)፦ ግንቦት 28 ቀን 2013 ዓ.ም. እንደሚካሔድ የሚጠበቀው ስድስተኛው አገር አቀፍ ምርጫ 2013 በሦስት ሳምንታት ሊራዘም እንደሚችል የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአውሮፓ ሕብረትና የኢትዮጵያ ፍጥጫ

European Union Flag

ሕብረቱ ምርጫውን አልታዘብም ሲል
ኢትዮጵያ ሕብረቱ ሉዓላዊነትን የሚጋፋ ጥያቄ በማቅረቡ ትከሳለች
በምርጫው ታዛቢ ላለመላክ የተፈለገውም ኢትዮጵያ ሉዓላዊነቴን የሚጋፋ አካሔድ አልቀበልም በማለቷ ነው

ኢዛ (ማክሰኞ ሚያዝያ ፳፮ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. May 4, 2021)፦ የአውሮፓ ሕብረት በኢትዮጵያ የሚካሔደውን አገር አቀፍ ምርጫ 2013 ታዛቢዎቹን እንደማይልክ አስታወቀ። ውሳኔውን የኢትዮጵያ መንግሥት ያልተገባ ብሎታል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በዘጠኝ ወር 55.8 ቢሊዮን ብር ገቢ አገኘ

Commercial Bank of Ethiopia

13.4 ቢሊዮን ብር አትርፏል

ኢዛ (ረቡዕ ሚያዝያ ፳ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. April 28, 2021)፦ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ2013 ዓ.ም. በጀት ዓመት በዘጠኝ ወራት ከ55.8 (ሃምሳ አምስት ነጥብ ስምንት) ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ማሰባሰቡን እና ከታክስ በፊት 13.4 (አሥራ ሦስት ነጥብ አራት) ቢሊዮን ብር ማትረፉን አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አርቲስት መስፍን ጌታቸው አረፈ

Mesfin Getachew

ለሞት የዳረገው ኮቪድ 19 ነው

ኢዛ (እሁድ ሚያዝያ ፲፯ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. April 25, 2021)፦ በኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ 19) ምክንያት ታምሞ በኤካ ኮተቤ ሆስፒታል የሕክምና እርዳታ ሲደረግለት የቆየው አርቲስት መስፍን ጌታቸው በተወለደ 50 ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ሥራ አስፈጻሚ ከኃላፊነታቸው አለመነሳታቸውን አስታወቁ

Mulu Nega

ዶ/ር ሙሉ ነጋ በክልሉ ያሉ ወጣት አመራሮችን አላግባብ ከኃላፊነታቸው አንስተዋል ተብለው ይታማሉ

ኢዛ (ረቡዕ መጋቢት ፳፱ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. April 7, 2021)፦ በፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔና በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ የጸደቀውን የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር በዋና ሥራ አስፈጻሚነት እየመሩ ያሉት ዶ/ር ሙሉ ነጋ ከኃላፊነታቸው መነሳታቸው በማኅበራዊ ትስስር ገጾች የተነገረ ቢኾንም፤ እሳቸው ግን በሥራ ላይ እንደሚገኙና ከኃላፊነታቸው ስለመነሳታቸው እንደማያውቁ መግለጻቸው ተነገረ። ተሰማ። ዶ/ር ሙሉ በክልሉ ያሉ ወጣት አመራሮችን ከኃላፊነታቸው አንስተዋል ተብለው ይታማሉ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአልሲሲ ድምፅ ከካይሮ - ጠብታ ውኃ አይወሰድብኝም እያለ ነው

President Abdul Fattah al-Sisi

ለማስጠንቀቅም ዳድተዋል

ኢዛ (ማክሰኞ መጋቢት ፳፩ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. March 30, 2021)፦ በታላቁ ህዳሴ ግድብና በዓባይ ውኃ አጠቃቀም ዙሪያ ድምፃቸው ብዙም የማይሰማው የግብጹ አብዱል ፈታህ አልሲሲ ዛሬ ማክሰኞ መጋቢት 21 ቀን 2013 ዓ.ም. ማስጠንቀቂያ አዘል መልእክት አስተላልፈዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ በኦነግ ላይ ውሳኔ አሳለፈ

ምርጫ ቦርድ (ዓርማ)፣ አቶ ዳውድ ኢብሳ (በቀኝ)፤ አዲስ የተመረጡትና ምርጫ ቦርድ እውቅና የነፈጋቸው ሥስቱ አመራሮች (በግራ)

በቅርቡ ጠቅላላ ጉባዔ ያካሔደው ኦነግ ተቀባይነት የሌለው ነው ብሏል
አዳዲሶቹን አመራሮች ተቀባይነት የላቸውም በማለት ውሳኔ አሳልፏል
በምርጫው እንሳተፍ የሚለው ጥያቄያቸውም ውድቅ ኾኗል

ኢዛ (እሁድ መጋቢት ፲፱ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. March 28, 2021)፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በቅርቡ የተካሔደውን የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (የኦነግ) ጠቅላላ ጉባዔ እና የተመረጡትን አዳዲስ አመራሮች ተቀባይነት የሌለው መኾኑን ውሳኔ አሳለፈ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኤርትራ ሠራዊቷን ከኢትዮጵያ ድንበር ለማስወጣት ተስማማች

President Isaias Afwerki (L) and PM Abiy Ahmed (R)

የኢትዮጵያ ብሔራዊ የመከላከያ ሠራዊት ወዲያውኑ ተክቶ የድንበር አካባቢዎችን ይጠብቃል

ኢዛ (ዓርብ መጋቢት ፲፯ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. March 26, 2021)፦ ትናንት ወደ አስመራ ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት የተጓዙት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ፣ ከአቻቸው የኤርትራው ፕሬዝዳንት ጋር ባደረጉት ውይይት፤ ኤርትራ ሠራዊቷን ከኢትዮጵያ ድንበር ለማስወጣት መስማማትዋን ዛሬ አስታወቁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አስመራ ናቸው

PM Abiy Ahmed (L) and President Isaias Afwerki (R)

የኤርትራ ወታደሮች በትግራይ ፈጽመዋቸዋል በተባሉ ጥቃቶችና በኢትዮጵያ ግዛት ውስጥ ስላለው የኤርትራ ሠራዊት ይወያያሉ ተብሎ ተገምቷል

ኢዛ (ሐሙስ መጋቢት ፲፮ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. March 25, 2021)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ከፕሬዝዳንት ኢሳይያስ አፈወርቂ ጋር ለመምከር ወደ አስመራ ማቅናታቸው ተሰማ። በሕወሓት እና በፌዴራሉ መንግሥት መካከል ጦርነቱ ከተቀሰቀሰ ወዲህ ይህ የመጀመሪያው ኦፊሴላዊ ጉብኝታቸው ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በትግራይ ተፈጽሟል በተባለው የሰብአዊ መብት ጥሰት ኢሰመኮ እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በጋራ ለመመርመር ተስማሙ

EHRC and OHCHR

ምርመራቸውን በአጭር ጊዜ ለመጀመር ወስነዋል

ኢዛ (ሐሙስ መጋቢት ፲፮ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. March 25, 2021)፦ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን (ኢሰመኮ) እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብአዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽን (Office of the United Nations High Commissioner for Human Rights - OHCHR)፤ በትግራይ ክልል ተፈጽሟል የተባለውን የመብት ጥሰት በጋራ ለመመርመር ስምምነት ላይ መድረሳቸውን ሁለቱ ተቋማት በጋራ ባወጡት መግለጫ አስታወቁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ