ሩብ ያህሉ የኢትዮጵያ መሬት ለውጭ ዜጎች ሊሸጥ ነው

የሕንድና የሳውዲ ባለሀብቶች ኢትዮጵያ ናቸው

Ethiopia Zare (አርብ ኅዳር 4 ቀን 2002 ዓ.ም. November 13, 2009)፦ በኢትዮጵያ ለእርሻ አገልግሎት ከሚውለው 14 ሚሊዮን ሔክታር መሬት ውስጥ ከሦስት ሚሊዮን በላይ የሚሆነው ለውጭ ባለሀብቶች እንደሚሸጥ የግብርና ኢንቨስትመንት ኤጀንሲ አስታውቋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ፕ/ር ኤፍሬም ፖለቲከኞቹን ይቅር ሊያባብሉ ከላይ ታች እያሉ ነው

Ethiopia Zare (አርብ ኅዳር 4 ቀን 2002 ዓ.ም. November 13, 2009)፦ የቅንጅት እስረኞችን በማስፈታት ዓይነተኛ ሚና ተጫውቷል የሚባለው በፕሮፌሠር ኤፍሬም ይስኃቅ የሚመራው የሽማግሌዎች ቡድን መድረክንና ኢህአዲግን ለመሸምገል ከታች ከላይ ማለት መጀመራቸውን የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ለወ/ት ብርቱካን ቤተሰቦች መርጃ በሲያትል የራት ምሽት ተዘጋጀ

ድምጻዊ ሻምበል በላይነህ የሙዚቃ ዝግጅት ያቀርባል

Ethiopia Zare (ሐሙስ ኅዳር 3 ቀን 2002 ዓ.ም. November 12, 2009)፦ ገቢው ሙሉ ለሙሉ በእስር ለምትገኘው የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ሊቀመንበር ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ ቤተሰቦች መርጃ የሚሆን የራትና የሙዚቃ ምሽት በሲያትል አካባቢ የሚገኙ ወጣቶች ከሲያትል አንድነት ጋር በመተባበር ማዘጋጀታቸው ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የዶ/ር ብርሃኑ ነጋ እና የአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ንብረት ሊታገድ ነው

በእነ ብ/ጄ/ል ተፈራ ማሞ ላይ የጥፋተኝነት ውሳኔ ለመስጠት ህዳር 4 ተቀጠረ

Ethiopia Zare (ሐሙስ ጥቅምት 26 ቀን 2002 ዓ.ም. November 5, 2009)፦ ከግንቦት 7 ንቅናቄ ጋር በተያያዘ “እነ ብርጋዲየር ጄነራል ተፈራ ማሞ” በሚል መዝገብ ክስ ከመሰረተባቸው 46 ግለሰቦች ውስጥ ዓቃቤ ሕግ የስምንቱ ንብረት እንዲታገድለት ጠይቆ ፍርድ ቤቱ ፈቀደለት። ንብረታቸው የታገደባቸው ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ፣ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ፣ ኮሎኔል አለሁበል አማረ እና አቶ ያረጋል ይማሞ በሌሉበት ሲሆን፤ በእስር ከሚገኙት ውስጥ ደግሞ ብ/ጄ/ል ተፈራ ማሞ፣ አቶ ፅጌ ኃብተማርያም (የአቶ አንዳርጋቸው አባትና የ80 ዓመቱ አዛውንት)፣ አቶ አሳምነው ፅጌ እና አቶ ጌቱ ወርቁ (የዶ/ር ብርሃኑ የቅርብ ዘመድ) ናቸው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የእስልምና ጉዳዮች ፕሬዝዳንትና ሌሎች አመራሮች ኢህአዲግ ስላልሆንን ተባረርን አሉ

Ethiopia Zare (ረቡዕ ጥቅምት 18 ቀን 2002 ዓ.ም. October 28, 2009)፦ የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሐጅ ባህር አብደላ እና ሁለት ከፍተኛ አመራሮች በሰባት ወር ዕድሜያቸው ሥልጣናቸውን ያጡት የኢህአዴግ አባል አንሆንም በማለታቸው መሆኑን ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...