በስዊድን የአውሮፓ የውጪ ጉዳይ ሚንስትሮች በተሰበሰቡበት ሠላማዊ ሰልፍ ተደረገ

ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ እንድትፈታ ተጠየቀ

በስቶክሆልም ሴፕቴ. 5 ቀን 2009 ሠላማዊ ሰልፈኞች

በማትያስ ከተማ

Ethiopia Zare (ሰኞ ጳጉሜን 2 ቀን 2001 ዓ.ም. September 7, 2009)፦ ባለፈው ቅዳሜ ነሐሴ 30 ቀን 2001 ዓ.ም. (September 5, 2009) ”ሼፕስሆልመን” በሚባለውና በስቶኮልም ግራንድ ሆቴል አጠገብ በሚገኝ የስብሰባ ቦታ የአውሮፓ የውጪ ጉዳይ ሚንስትሮች ሰብሰባ ተጀምሯል። በስቶክሆልምና አካባቢው የሚገኙ በርካታ ኢትዮጵያውያን በስፍራው በመገኘት ሠላማዊ ሰልፍ ከማድረጋቸውም በላይ ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ ካለምንም ቅድመ ሁኔታ በአስቸኳይ ትፈታ ዘንድ መልዕክታቸውን ለተሰብሳቢዎቹ አሰምተዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ቀነኒሳ በቀለ አንድ ሚሊዮን ዶላሩን ተቋደሰ

ገንዘቡን ከይሌና ኢሲንባዬቫ እና ከሳንያ ሪቻርድስ ጋር ይካፈላል

አትሌት ገለቴ ቡርቃ በ2000 ሜትር አንደኛ ወጣች

(ተጨማሪ ዘገባና ፎቶዎች የታከለበት)

Kenenisa Bekele crosses the finish line to win the men's 5000m race at the IAAF Golden League Memorial Van Damme athletics meeting in Brussels September 4, 2009.

Ethiopia Zare (ዓርብ ነሐሴ 29 ቀን 2001 ዓ.ም. September 4, 2009)፦ ከአስር ደቂቃ በፊት ዛሬ ዓርብ ነሐሴ 29 ቀን 2001 ዓ.ም. ማምሻውን በቤልጅየም ብራስልስ እየተደረገ ባለው የ2009ኙ የጎልደን ሊግ 6ኛና የመዝጊያው ውድድር ላይ ቀነኒሳ በቀለ በ5000 ሜትር በአንደኝነት በማጠናቀቅ የአንድ ሚሊዮን ዶላሩ ጃክ ፖት ተቋዳሽነቱን አረጋገጠ። ውድድሩን በ12 ደቂቃ ከ55፡31 ሰከንድ ነው የጨረሰው። አንድ ሚሊዮን ዶላሩን ከራሺያዊቷ የምርኩዝ ዘላይዋ ይሌና ኢሲንባዬቫ እና ከአሜሪካዊቷ የ400 ሯጭ ሳንያ ሪቻርድስ ጋር ይካፈላል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

መድረክ ስብሰባውን ረግጦ ወጣ

Dr. Merera and Prof. BeyeneEthiopia Zare (ኀሙስ ነሐሴ 28 ቀን 2001 ዓ.ም. September 3, 2009)፦ በእንግሊዝ ኤምባሲ አግባቢነት መጪውን የ2002 ዓ.ም. የሀገር አቀፍ ምርጫን አስመልክቶ በተቃዋሚዎችና በገዥው ፓርቲ መካከል የተጀመረውን ስብሰባ መድረክ (መድረክ ለዲሞክራሲያዊ ምክክር በኢትዮጵያ) ዛሬ (ኀሙስ ነሐሴ 28 ቀን 2001 ዓ.ም.) ረግጦ ወጣ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኢ.ቴ.ቪ ጋዜጠኞችና የአንድነት ደጋፊዎች በሐዋሳ ተጋጩ

Ethiopia Zare (ኀሙስ ነሐሴ 28 ቀን 2001 ዓ.ም. September 3, 2009)፦ ባለፈው እሑድ ነሐሴ 24 ቀን 2001 ዓ.ም. በሐዋሳ ከተማ አንድነት ፓርቲ ህዝባዊ ስብሰባውን ያካሄደ ሲሆን፣ በቦታው የተገኙ የኢ.ቴ.ቪ. ጋዜጠኞችና የፓርቲው ደጋፊዎች ጋር ግጭት ፈጥረው ስብሰባውን ሳይቀርጹ መመለሳቸውን የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በአተት ምክንያት ምግብ ቤቶች እየታሸጉ ነው

Ethiopia Zare (ኀሙስ ነሐሴ 28 ቀን 2001 ዓ.ም. September 3, 2009)፦ በሀገሪቱ ውስጥ በቅርቡ የተከሰተውን የአጣዳፊ ተቅማጥና ተውከት (አተተ) በሽታ ለመከላከል በሚል የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር በአንዳንድ አገልግሎት ሰጪ የአዲስ አበባ ሆቴሎችንና ምግብ ቤቶችን በማሸግ ላይ መሆኑ ተገለፀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአንድነት መሪ ወ/ት ብርቱካን የዓመቱ ድንቅ ሰው ተብላ ተሸላሚ ሆነች

Ethiopia Zare (ረቡዕ ነሐሴ 27 ቀን 2001 ዓ.ም. September 2, 2009)፦ የሕግ የበላይነትን፣ ዲሞክራሲንና ነፃነትን በግል ሕይወቷ ላይ ተግባራዊ ያደረገችው የመጀመሪያዋ ኢትዮጵያዊት የፖለቲካ ፓርቲ መሪ ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ የ2001 ዓ.ም. የዓመቱ ድንቅ ሰው ሽልማት አሸናፊ ሆነች።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የጅምላ ግድያ፣ ዝርፊያና የአስገድዶ መድፈር ወንጀል በፈጸሙ ሰዎች ላይ ውሳኔ ሊሰጥ ነው

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ነሐሴ 26 ቀን 2001 ዓ.ም. September 1, 2009)፦ የፌደራሉ ከፍተኛው ፍርድ ቤት 2ኛ የወንጀል ችሎት፤ ከአንድ ዓመት በፊት በምሥራቅ ወለጋ በሚገኙ ሦስት የቤኒሻንጉል ጉምዝ “ክልል” አዋሳኝ ሥፍራዎች “የግድያ፣ የዝርፊያ፣ የአስገድዶ መድፈርና የንብረት ማውደም ወንጀል ፈጽመዋል” ባላቸው 101 ተከሳሾች ላይ የመጨረሻ የቅጣት ውሳኔ ለማስተላለፍ ለነሐሴ 27 ቀን 2001 ዓ.ም. ተለዋጭ ቀጠሮ ይዟል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢህአዲግ ከተቃዋሚዎች ጋር ለመደራደር ዝግጁ መሆኑን ገለጸ

Ethiopia Zare (ቅዳሜ ነሐሴ 23 ቀን 2001 ዓ.ም. August 29, 2009)፦ በመጪው ሰኞ ነሐሴ 25 ቀን 2001 ዓ.ም. የኢትዮጵያው ገዢ ፓርቲ (ህወሓት/ኢህአዲግ) በሀገር ውስጥ አሉ ከሚባሉት “ዋንኛ” የሚባሉ ተቀናቃኝ ፓርቲዎች ጋር ውይይት እንደሚያካሂድ ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ቀነኒሳ በቀለ አምስተኛውን የጎልደን ሊግ ወርቅ አገኘ

Kenenisa Bekele sets a World Leading 5000m time of 12:52.32 in Zurich. (Getty Images)የአንድ ሚሊዮን ዶላሩን ጃክ ፖት ለመቋደስ አንድ ውድድር ይቀረዋል

Ethiopia Zare (ዓርብ ነሐሴ 22 ቀን 2001 ዓ.ም. August 28, 2009)፦ በዛሬው ዕለት ማምሻውን በስዊዘርላንድ ዙሪክ ከተማ በተደረገው የ2009ኙ የጎልደን ሊግ 5ኛ ዙር ውድድር ላይ ቀነኒሳ በቀለ በ5000 ሜትር አንደኛ በመሆን ውድድሩን አሸነፈ። የአንድ ሚሊዮን ዶላሩን ጃክ ፖት ለመቋደስ ከቀሩት ሦስት አትሌቶች ውስጥ አንዱ ሆኗል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...