መኢአድ በአፋር መንግሥት ተብጠለጠለ

‘የተቃወመው የአፋር ህዝብ አይደለም’ ኢንጂኒየር ኃይሉ ሻውል

Ethiopia Zare (ዓርብ ነሐሴ 7 ቀን 2001 ዓ.ም. August 14, 2009)፦ መኢኣድ ባለፈው እሁድ በዳግማዊ ምኒልክ ባደረገው ህዝባዊ ስብሰባ የተወካዮች ምክር ቤት ያፀደቀውን የሠንደቅ ዓላማ ዓርማ ለመጀመሪያ ጊዜ በአደባባይ የተቃወመ ሲሆን፣ የአፋር ክልላዊ መንግሥት ዓርማውን መቃወም የብሔረሰቦችን መብት መቃወም ነው ሲል መግለጫ አውጥቷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ስዊድን ውስጥ ኢትዮጵያዊት ስደተኛ ተገደለች

Melete Kahssay, 25 ወ/ት ምልዕተ ካህሳይ ገዳይዋ ለፖሊስ እጁን ሰጠ

Ethiopia Zare (ሐሙስ ነሐሴ 7 ቀን 2001 ዓ.ም. August 13, 2009)፦ በስዊድን ዋና ከተማ ስቶክሆልም በስደት ትኖር የነበረችና ወ/ት ምልዕተ ካህሳይ የተባለች የ25 ዓመት ወጣት ኢትዮጵያዊት ባለፈው ሣምንት ረቡዕ ዕለት የተገደለች ሲሆን፤ ገዳይዋም በማግስቱ እጁን ለፖሊስ መስጠቱን የኢትዮጵያ ዛሬ ሪፖርተር ዘገበ። 

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ቴዲ አፍሮ ዛሬ ማምሻውን ከእስር ተለቀቀ

Teddy Afro ቴዲ አፍሮ
 

Ethiopia Zare (ሐሙስ ነሐሴ 7 ቀን 2001 ዓ.ም. August 13, 2009)፦ ላለፉት 484 ቀናት በእስር የቆየው ወጣቱ እውቅ አርቲስት ቴዎድሮስ ካሣሁን (ቴዲ አፍሮ) ዛሬ ሐሙስ ነሐሴ 7 ቀን 2001 ዓ.ም. በኢትዮጵያ አቆጣጠር ከምሽቱ 12፡30 አካባቢ ከእስር መለቀቁን የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ትናንት ይፈታል ተብሎ የነበረው ቴዲ አፍሮ ሳይፈታ ቀረ

Teddy Afro ቴዲ አፍሮ መጻሕቶቹን ለላይብረሪ፣ ልብሶቹን ለእስረኞች አከፋፈለ

Ethiopia Zare (ሐሙስ ነሐሴ 7 ቀን 2001 ዓ.ም. August 13, 2009) ታዋቂው ድምጻዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ትናንት ረቡዕ ነሐሴ 6 ቀን 2001 ዓ.ም. ጠዋት ከእስር እንደሚለቀቅ በስፋት ተወርቶ የነበረ ቢሆንም፤ አድናቂዎቹና ቤተሰቦቹ ቃሊቲ እስር ቤት ሄደው ለረዥም ሰዓታት ሲጠባበቁ ከቆዩ በኋላ ባዷቸውን ተመልሰዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

”ጠንቋይ” ታምራት ገለታ በሁሉም ክሶች ጥፋተኛ ተባለ

ዓቃቤ ሕግ በሞት ይቀጣልኝ ሲል ጠየቀ

Ethiopia Zare (ረቡዕ ነሐሴ 6 ቀን 2001 ዓ.ም. August 12, 2009)፦”ባለአውሊያ” እና ”ባለከራማ” ነኝ በማለት ከአሥር ዓመት በላይ በጥንቆላ ሥራ ላይ ተሰማርቶ የነበረው አቶ ታምራት ገለታን ዛሬ ረቡዕ ነሐሴ 6 ቀን 2001 ዓ.ም. የዋለው የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 2ኛ ወንጀል ችሎት ”ጥፋተኛ” ያለው ሲሆን፣ ንብረቶቹም ተወርሰው ለመንግሥት ገቢ እንዲሆኑ ወሰነ። ዓቃቤ ሕግ በሞት ይቀጣልኝ አለ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ታዋቂው ጠበቃ አበበ ወርቄ የአንድ ዓመት እስራት ተፈረደባቸው

ፍርዱ ከአሜሪካን ወደ ኢትዮጵያ እንዳይመለሱ ለማድረግ እንደሆነ ተጠቁሟል

Ethiopia Zare (ሐሙስ ሐምሌ 30 ቀን 2001 ዓ.ም. August 6, 2009)፦ ለሕክምና በአሜሪካ ሀገር በሚገኙት ታዋቂው ጠበቃ አበበ ወርቄ ላይ የፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት 8ኛ ወንጀል ችሎት ከኤቢሲ ብሮድካስቲን ጋር በተያያዘ የአንድ ዓመት እስራትና የገንዘብ ቅጣት ወሰነባቸው። ቅጣቱ አቶ አበበን ወደ ሀገር ቤት እንዳይመለሱ ለማድረግ ነው ሲሉ በአዲስ አበባ የሚገኙ የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች ገለፁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

እነ ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ጥፋተኛ ተባሉ

ከግንቦት 7 ጋር በተያያዘ ከ46ቱ ተከሳሶች በእስር የሚገኙት 32ቱም ይከላከሉ ተባሉ፣

በሌሉበት ከተከሰሱት 13ቱ ጥፋተኛ ተባሉ

Ethiopia Zare (ሐሙስ ሐምሌ 30 ቀን 2001 ዓ.ም. August 6, 2009)፦ ዛሬ ሐሙስ ሐምሌ 30 የዋለው የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 2ኛ ወንጀል ችሎት፤ ከግንቦት 7 ጋር በተያያዘ ክስ የተመሰረተባቸው ተከሳሾች ውስጥ የግንቦት 7 መሥራቾችና መሪዎች በሆኑት በእነ ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ እና በአቶ አንደርጋቸው ጽጌ ላይ የጥፋተኝነት ፍርድ ሰጠ። በእስር ላይ ከሚገኙት 32 ተከሳሾች ውስጥ 29ኙን በቀረቡባቸው 5ቱም ክሶች እንዲከላከሉ ብይን ሰጥቷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የታገዱት 21ዱ የአንድነት ከፍተኛ አመራሮች መግለጫ አወጡ

Ethiopia Zare (ረቡዕ ሐምሌ 29 ቀን 2001 ዓ.ም. August 5, 2009)፦ ፕ/ር መስፍንን ጨምሮ 21ዱ የታገዱት የአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራር አባላት “የአንድነት ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ በሥልጣን መባለግ” በሚል በተከታታይ ሲያወጡት የነበረውን መግለጫ ክፍል ሦስት አወጡ። ይኸው መግለጫ “በአንድነት ፓርቲ ውስጥ ደንባዊና ተቋማዊ አሠራር ሲፈተሽ” የሚል ንዑስ ርዕስ ሰጥተውታል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ካናዳዊ በኢትዮጵያ በሽብርተኝነት የዕድሜ ልክ እስራት ተፈረደበት

Bashir Mukhtal, አቶ በሽር ሙኽታልEthiopia Zare (ሰኞ ሐምሌ 27 ቀን 2001 ዓ.ም. August 3, 2009)፦ የኢትዮጵያ ተወላጅ የሆነውና የካናዳ ዜግነት ያለው አቶ በሽር ሙኽታል በኦብነግ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነትና በሽብር ወንጀል ተጠርጥሮ ክስ ተመስርቶበት ሲከራከር ከቆየ በኋላ፤ ዛሬ ሰኞ ሐምሌ 27 ቀን 2001 ዓ.ም. የዋለው የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 2ኛ ወንጀል ችሎት የዕድሜ ልክ ፅኑ እስራት እንደፈረደበት የኢትዮጵያ ዛሬ ሪፖርተር ከአዲስ አበባ ዘገበ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

መንግሥት “ተሰወሩ” ያላቸውን የጤና ባለሙያዎች እየፈለገ ነው

Ethiopia Zare (ዓርብ ሐምሌ 24 ቀን 2001 ዓ.ም. July 31, 2009)፦ የጤና ጥበቃ መ/ቤት፤ ሙያዊ ኃላፊነታቸውን አልተወጡም፣ መንግሥትና ህዝብ ከእነሱ የሚጠብቀውን ተግባር አልፈጸሙም በማለት በርካታ የጤና ባለሙያዎች ሕግ ፊት ለማቅረብ እንደሚፈልጋቸው አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...