ሰባት የመንግሥት ድርጅቶች በ780 ቢሊዮን ብር እዳ መዘፈቃቸው ተረጋገጠ

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት፣ የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን፣ ሜቴክ (አሁን ኢትዮ-ኢንጂነሪንግ ግሩፕ)፣ ኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን፣ የኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን እና የስኳር ኮርፖሬሽን

የአብዛኛውን ብድር የወሰዱት ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ነው

ኢዛ (ዓርብ መጋቢት ፲፯ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. March 26, 2021)፦ ከፍተኛ የአገር ውስጥ ብድር ካለባቸው የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ውስጥ ሰባቱ ብቻ ከ780 ቢሊዮን ብር በላይ (ከ19 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ) እዳ እንዳለባቸው ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ዛሬ የመራጮች ምዝገባ ተጀመረ

National Election Board of Ethiopia (NEBE)

50 ሺህ የምርጫ ጣቢያዎች፣ ከ152 ሺህ የመራጮች ምዝገባ የሚያካሒዱ ባለሙያዎች እና ከ254 ሺህ በላይ የምርጫ አስፈጻሚዎች ተዘጋጅተዋል

ኢዛ (ሐሙስ መጋቢት ፲፮ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. March 25, 2021)፦ የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ስድስተኛውን አገራዊ ምርጫ (ምርጫ 2013) ለማካሔድ ከሚጠበቁበት ክንውኖች አንዱ የኾነውን እና ለ30 ቀናት የሚቆየውን የመራጮች ምዝገባ ዛሬ መጀመሩን አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአማራ ብልጽግና ፓርቲ ጠንከር እና መረር ያለ መግለጫ አወጣ

Prosperity Party

- የአማራና የኦሮሞ ሕዝብ ከብልጽግና ፓርቲም በላይ ነው
- የኦሮሚያ ብልጽግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤትን ጨምሮ ሁሉም የዴሞክራሲ ኃይሎች ለችግሩ ተደማሪ ችግር ከመኾን ይልቅ መፍትሔው ላይ በመተባበርና በመረባረብ ዘላቂ መፍትሔ እንዲመጣ መታገል ይኖርብናል

ኢዛ (ሐሙስ መጋቢት ፲፮ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. March 25, 2021)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ማብራሪያ የሰጡበትንና ባለፈው ማክሰኞ መጋቢት 14 ቀን የተካሔደውን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ስብሰባን ተከትሎ፤ የአማራ ብልጽግና ፓርቲ ጠንከር እና መረር ያለ መግለጫ አውጥቷል። በተለይም በሰሜን ሸዋ የደረሰው እልቂት “በኦሮሞ ዘር ላይ ያተኮረ” ነው ያሉ የኦሮሞ ብልጽግና የፓርላማ አባላትን ተከትሎ መግለጫው እንደወጣ ተገምቷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

እነ ጃዋር መሐመድ የእምነት ክህደት ቃላቸውን ሰጡ

Jawar Mohammed (L), Bekele Gerba (M) and Hachalu Hundessa (R)

በተከሰሱበት ክስ ጥፋተኛ አይደለንም አሉ

ኢዛ (ሰኞ መጋቢት ፲፫ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. March 22, 2021)፦ ከአርቲስት ሐጫሉ ሁንዴሳ ግድያ ጋር ተያይዞ በተለያዩ የኦሮሚያ ክልል ከተሞች በተፈጠረው ኹከት በመጠርጠር በቁጥጥር ሥር የዋሉት እነ አቶ ጃዋር መሐመድ ዛሬ ፍርድ ቤት ቀርበው የእምነት ክህደት ቃላቸውን ሰጥተዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ነገ ለፓርላማው ማብራሪያ ይሰጣሉ

PM Abiy Ahmed

በወቅታዊ አገራዊ ጉዳዮች ከምክር ቤቱ አባላት ለሚቀርቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽ ይሰጣሉ

ኢዛ (ሰኞ መጋቢት ፲፫ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. March 22, 2021)፦ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በነገው ዕለት ጠቅላይ ሚኒስተር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ በወቅታዊ አገራዊ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ ይሰጡበታል የተባለው መደበኛ ስብሰባውን ያካሔዳል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አፋሮች ለጄኔራሎቹ ከፍተኛ የጦር ሜዳ ኒሻን ሸለሙ

የአፋር ክልላዊ መንግሥት ርዕሰ መስተዳድር አቶ አወል አርባ ለመከላከያ ዋና ኤታማዦር ሹም ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ ኒሻኑን ሲያበረክቱ

ቤት መሥሪያ ቦታም ተበርክቶላቸዋል

ኢዛ (ሰኞ መጋቢት ፲፫ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. March 22, 2021)፦ በትግራይ ክልል በተካሔደው የሕግ ማስከበር ዘመቻ በስኬት ለመሩት የጦር መሪዎች “መላሳይ” የተባለ የጦር ማዕረግ ስያሜ የያዘ የክብር ኒሻን እና የቤት መሥሪያ ቦታ ከአፋር ክልላዊ መንግሥት ተሸለሙ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የእነአቶ ስብሃት ነጋ አቤቱታ እና ተለዋጨ ቀጠሮ

Sebhat Nega

ጠበቆች ማስጠንቀቂያ ተሰጣቸው

ኢዛ (ሰኞ መጋቢት ፲፫ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. March 22, 2021)፦ በዛሬው ዕለት ከቀድሞ የሕወሓት ከፍተኛ አመራሮች ውስጥ አቶ ስብሃት ነጋ፣ አዲስ ዓለም ባሌማ፣ አምባሳደር አባይ ወልዱ እና ሌሎች ተጠርጣሪዎች በዛሬው ቀጠሮ ፍ/ቤት ቀርበዋል። ፍ/ቤት የቀረቡት የዓቃቤ ሕግ የቅድመ ምርመራ ምስክር ለመስማት ሲሆን፤ ተጠርጣሪዎቹ የተለያዩ አቤቱታዎችን ያቀረቡበት ኾኗል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ነዋሪዎች የጸጥታ ሥጋት እንዳለባቸው እየገለጹ ነው

Shew Robit town

በሸዋ ሮቢት አገልግሎት መስጫ ተቋማት ተዘግተው ውለዋል

ኢዛ (ሰኞ መጋቢት ፲፫ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. March 22, 2021)፦ ከሰሞኑ የሰው ሕይወት የቀጠፈው፣ ሀብት እና ንብረት ያወደመው የአጣየ እና የአጎራባች አካባቢዎች ጥቃትን ተከትሎ የተፈጠረው የጸጥታ ችግር አሁንም ያለ ሲሆን፤ በዛሬው ዕለት የእንደ ሸዋ ሮቢት ያሉ ከተሞች የተለያዩ አገልግሎት ተቋማት ተዘግተው ውልውዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ተኩስ አሁንም አለ

አቶ ሲሳይ ዳምጤ

ታጣቂ ቡድኑ ከአጣየ ውጭ ጥቃቱን ለማስፋት እየሞከረ ነው ተባለ
ሕዝቡ ነገሮችን በትእግሥት እንዲመለከት ተጠየቀ

ኢዛ (እሁድ መጋቢት ፲፪ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. March 21, 2021)፦ በአጣየና በአካባቢው በተደራጀ ሁኔታ ጥቃት ያደረሰው የታጠቀ ኃይል አሁንም ተኩስ መግጠሙንና ጥቃቱን ወደ ማጀቴ፣ ሰንበቴና ሸዋ ሮቢት አካባቢዎች ለማስፋት እየሞከረ መኾኑን የአማራ ክልል ሰላምና ደኅንነት ቢሮ ኃላፊ ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሠራዊቱን የማይወክል ተግባር የፈጸሙ ተጠያቂ እንደሚኾኑ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አሳሰቡ

PM Abiy Ahmed

በአግባቡ የሚሠሩትን ደግሞ መሸለም ይገባል አሉ

ኢዛ (እሁድ መጋቢት ፲፪ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. March 21, 2021)፦ በየትኛውም የሕግ ማስከበር ተግባር የመከላከያ ሠራዊታችንን እሴቶች የማይወክል ተግባር የሚፈጽሙትን ተጠያቂ ማድረግ፤ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ የሚወጡትን መሸለም እንደሚገባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ