የመንገደኞች ንብረት ዝርፊያ - በኢትዮጵያ አየር መንገድ

15 ሠራተኞች በቁጥጥር ስር ዋሉ

Ethiopia Zare (እሁድ ሰኔ 29 ቀን 2000 ዓ.ም. July 6, 2008)፦ በኢትዮጵያ አየር መንገድ የሚጓጓዙ መንገደኞች ከየሻንጣቸው ውስጥ ንብረቶቻቸው እንደሚጠፋባቸው ማማረር ከጀመሩ ቆየት ብሏል። ዝርፊያው ለስድስት ወር ያህል የዘለቀ ነበር። ብዙውን ጊዜ ንብረት ከጠፋባቸው መንገዶኞች መካከል ጠንከር ብሎ ጥያቄውን ያቀረበ ንብረቱ በገንዘብ እየተቀየረ ይከፈለዋል፤ የፈራና የጣልኩት ሌላ ቦታ ነው ብሎ የጠረጠረ ደግሞ እንደጠፋበት ይቀራል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ቴዲ አፍሮ ዛሬም አልተፈታም

የተጭበረበረ ሰነድ እንዲጣራ ለሣምንት ተቀጥሯል

ሁለት ጋዜጠኞች ታሰሩ

Teddy AfroEthiopia Zare (ዓርብ ሰኔ 27 ቀን 2000 ዓ.ም. July 4, 2008)፦ ዛሬ ድምጻዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን እንደሚፈታ በአዲስ አበባ ውስጥ ወሬ ሲናፈስ የሰነበተ ቢሆንም ብይኑ ለሣምንት ተቀጥሯል። በዳግማዊ ምኒሊክ ሆስፒታል ዶ/ር የተፈረመበት የሟች ደጉ ይበልጣል የሞት የምስክር ወረቀት ቴዲ ከተከሰሰበት ቀን ጋር ልዩነት በመፍጠሩ ዳኛው ዛሬ ብይን መስጠት ሲገባቸው እስኪጣራ ለሣምንት ቀጠሮ በመስጠት ችሎቱን መበተናቸውን የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሰርካለምና ሲሳይ አሳታሚዎች ቅጣታቸውን እንዲከፍሉ ትዕዛዝ ወጣባቸው

አሳታሚዎቹ 300 ሺህ ብር መክፈል አለባቸው

"ግፊቱ ቢበዛብንም ሀገራችንን ለቀን አንወጣም" ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ

"የሚመጣብንን ለመቀበል ዝግጁ ነን" ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና

Ethiopia Zare (ዓርብ ሰኔ 27 ቀን 2000 ዓ.ም. July 4, 2008)፦ ከምርጫ 97 ጋር በተያያዘ ከቅንጅት አመራሮች ጋር ታስረው ድርጅታቸው እንዲፈርስና በገደብ እንዲቀጡ የተወሰነባቸው አራት የጋዜጣ ድርጅቶች ውሳኔው ከተሰጠ ከ11 ወራት በኋላ በቅጣት የተወሰነባቸው ወደ 300 ሺህ ብር የሚጠጋ ገንዘብ ለመንግሥት እንዲያስገቡ ትዕዛዝ እንደወጣባቸው ምንጮች ገለፁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ተለዋጭ ቤት በኪራይ ሊሰጣቸው ነው

Dr. Negasso GidadaEthiopia Zare (ኀሙስ ሰኔ 26 ቀን 2000 ዓ.ም. July 3, 2008)፦ በአንድ ሣምንት ጊዜ ውስጥ የመኖሪያ ቤታቸውን ለቀው እንዲወጡ ተነግሯቸው የነበረው የቀድሞው የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ተለዋጭ ቤት በኪራይ መልክ ሊሰጣቸው እንደሆነ አስታወቁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በጅማ ዩኒቨርሲቲ አንድ ተማሪ በጩቤ ተገደለ

ተጠርጣሪው ጓደኛው ነው

Ethiopia Zare (ረቡዕ ሰኔ 25 ቀን 2000 ዓ.ም. July 2, 2008)፦ ወጣት ደጉ ተስፋዬ ሰኔ 13 ቀን 2000 ዓ.ም ከጅማ ዩኒቨርሲቲ ትምህርቱን አጠናቅቆ ወደ ቤተሰቦቹ ለመመለስ ጊዜያዊ የትምህርት ማስረጃውን ይዞ፣ ዕቃውን ሸክፎ መናኸሪያ ከደረሰ በኋላ፤ የሞባይል ስልኩ ጠፍቶበት ስለነበር ስልኩ መገኘቱን የሚገልጽ መልዕክት ደርሶት ወደ ግቢው ሲመለስ ነው ሦስት ቦታ በጩቤ ተወግቶ የተገደለው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አፋኙ የፕሬስ ሕግ ዛሬ ፀደቀ

HAPIUNESCO እና ከUNOHCHR ጋር በመተባበር ነገ ጠዋት በረቂቅ አዋጁ ላይ ሴሚናር አዘጋጅቶ ነበር

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ሰኔ 24 ቀን 2000 ዓ.ም. July 1, 2008)፦ ከአምስት ዓመት በፊት ኅዳር 25 1995 ዓ.ም. የተረቀቀውና፣ ጥር 5 ቀን 1995 ዓ.ም. (January 13, 2003) ይፋ ከተደረገበት ጊዜ ጀምሮ ከፍተኛ ተቃውሞ የቀረበበትና አፋኝ መሆኑ ሲነገርለት የነበረው አዲሱ የፕሬስ ሕግ ዛሬ በፓርላማው መጽደቁን ለኢትዮጵያ ዛሬ ከአዲስ አበባ የደረሰው መረጃ ጠቆመ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የቅንጅቱ የቀድሞ ፀሐፊ አቶ ሙሉነህ አሜሪካ ገቡ

Ato Muluneh Eyuel"ግንቦት 7 ንቅናቄን ሊቀላቀሉ ይችላሉ"

Ethiopia Zare (ሰኞ ሰኔ 23 ቀን 2000 ዓ.ም. June 30, 2008)፦ የቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ፓርቲ የቀድሞ ፀሐፊ አቶ ሙሉነህ እዩኤል በትናንትናው ዕለት ወደ አሜሪካ ማቅናታቸውን የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች አረጋገጡ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በዶ/ር ታዬ ይመራ የነበረው አንጋፋው ኢመማ ለመጨረሻ ጊዜ ተዘጋ

Ato Gemoraw Kassaአዲሱ/ተለጣፊው መምህራን ማኅበር የ12 ሚሊዮን ብር ሊወርስ ነው

Ethiopia Zare (ዓርብ ሰኔ 20 ቀን 2000 ዓ.ም. June 27, 2008)፦ ለሰላሳ ዘጠኝ ዓመታት በኢትዮጵያ ውስጥ ሲንቀሳቀስና በአንድ ወቅት በዶ/ር ታዬ ወ/ሠማያት ይመራ የነበረው አንጋፋው የኢትዮጵያ መምህራን ማኅበር ከ15 ዓመታት የፍርድ ቤት ሙግት በኋላ ለመጨረሻ ጊዜ በሰበር ችሎት እንዲዘጋ ተወሰነ። አዲሱ/ተለጣፊው የመምህራን ማኅበር ወደ 12 ሚሊዮን ብር የሚጠጋ ገንዘብ ወራሽ ሊሆን ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የጠ/ሚ/ር መለስ ዜናዊ አባት አረፉ

Aboy Zenawi Asres, 82የሕይወት ታሪካቸውን ይዘናል (ተጨማሪ ዘገባ)

PM Meles ZenawiEthiopia Zare (ኀሙስ ሰኔ 19 ቀን 2000 ዓ.ም. June 26, 2008)፦ የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ወላጅ አባት የሆኑት አቶ ዜናዊ አስረስ ትናንት ረቡዕ ሰኔ 18 ቀን 2000 ዓ.ም. ከዚህ ዓለም ማረፋቸውን የአዲስ አበባ የኢትዮጵያ ዛሬ ድረ ገጽ ምንጮች ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

“መድረክ ለዲሞክራሲያዊ ምክክር በኢትዮጵያ” ዛሬ ሀገር ውስጥ ተመሰረተ

መሥራቾቹ ኢዲኃሕ፣ ኦፌዲን፣ ሶዲኃቅ፣ ዓረና፣ ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳና አቶ ስዬ አብርሃ ናቸው

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ሰኔ 17 ቀን 2000 ዓ.ም. June 24, 2008)፦ በዛሬው ዕለት በሀገር ውስጥ የሚገኙት የኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ኃይሎች ሕብረት (ኢዲኃሕ)፣ የኦሮሞ ፌዴራሊስት ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ኦፌዲን)፣ የሶማሌ ዲሞክራሲያዊ ኃይሎች ቅንጅት (ሶዲኃቅ)፣ ዓረና ትግራይ ለዲሞክራሲና ለሉዓላዊነት (ዓረና) የተሰኙት በሀገር ውስጥ የሚንቀሳቀሱት ፓርቲዎች ከቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ እና ከአቶ ስዬ አብርሃ ጋር በመሆን “መድረክ ለዲሞክራሲያዊ ምክክር በኢትዮጵያ” (መዲምኢ) በሚል ስያሜ አብረው ለመሥራት መስማማታቸውን ለኢትዮጵያ ዛሬ የደረሰው ዘገባ አስረዳ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...