16 ዘይት መጭመቂያዎች ታሸጉ

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ግንቦት 26 ቀን 2000 ዓ.ም. June 3, 2008)፦ ከመርዛማ ዕፁ ጋር የምግብ ዘይት ቀላቅለው ሲያመርቱ የነበሩ 16 የዘይት መጭመቂያ ቤቶች መታሸጋቸውን ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር አስታወቀ። የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የድርጊቱ ፈፃሚዎች እስካሁን እንዳልተደረሰባቸውና ፋብሪካዎቹ ስለመታሸጋቸውም መረጃ እንደሌላቸው ገልጿል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ንዋይና ታማኝ በጋራ በስቶክሆልም የሙዚቃ ዝግጅት አሳዩ

 ንዋይ ደበበ በቅርቡ አዲስ ነጠላ ዜማ እንደሚለቅ ገለጸ

Neway Debebe & Tamagne Beyene, Stockholm, 20080530Ethiopia Zare (ቅዳሜ ግንቦት 23 ቀን 2000 ዓ.ም. May 31, 2008)፦ አርቲስት ንዋይ ደበበ እና ታማኝ በየነ በአንድነት በትናንትናው ምሽት በስዊድን ዋና ከተማ ስቶክሆልም የሙዚቃ ዝግጅታቸውን ለርካታ ኢትዮጵያውያንና ለጥቂት የሌሎች ሀገር ዜጎች ሲያሳዩ አመሹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የታሰሩት የአዲስ ነገር ጋዜጣ አዘጋጆች በዋስ ተለቀቁ

Ethiopia Zare (ቅዳሜ ግንቦት 23 ቀን 2000 ዓ.ም. May 31, 2008)፦ ትናንት ጠዋት በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አራት ፖሊሶች ከቢሯቸው ተወስደው የታሰሩት ሁለት የ”አዲስ ነገር” ጋዜጣ አዘጋጆች ረፋዱ ከሰዓት ላይ በዋስ መለቀቃቸውን ከአዲስ አበባ የደረሰን ሪፖርት አስረዳ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

"አንድነት" ፓርቲን የሚመሰርቱት የቀድሞ ላዕላይ ም/ቤት አባላት 18 ናቸው

አቶ ሙሉነህ ኢዮኤል እና ዶ/ር በፍቃዱ ደግፌ መሰብሰብ አቁመዋል

ሰኔ ሰባት ጠቅላላ ጉባዔው ይካሄዳል

Ethiopia Zare (ዓርብ ግንቦት 22 ቀን 2000 ዓ.ም. May 30, 2008)፦ በሀገራችን የምርጫ እና የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ በማይረሳው ምርጫ 97 ከፍተኛ የህዝብ ድጋፍ አግኝቶ የነበረው የ“ቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ፓርቲ” አመራሮች እና የላዕላይ ምክር ቤት አባላት ከምርጫው ማግስት ጀምሮ ሲከፋፈሉ መሰንበታቸው አይዘነጋም። ከዚሁ ጋር በተያያዘ አመራሮቹና የላዕላይ ምክር ቤቱ አባላት አሁን በስተመጨረሻ ክፍፍሉ መስመር እየያዘና እየጠራ በመምጣት ላይ እንደሚገኝ አንዳንድ መረጃዎች ይጠቁማሉ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአዲስ ነገር ጋዜጣ ዋና አዘጋጅና ም/ዋና አዘጋጅ ታሰሩ

አቶ አየለ ጫሚሶ አራተኛ ጋዜጣ ከሰሱ

Ethiopia Zare (ዓርብ ግንቦት 22 ቀን 2000 ዓ.ም. May 30, 2008)፦ በየሣምንቱ ቅዳሜ መታተም ከጀመረ 32 ሣምንታትን ያስቆጠረው “አዲስ ነገር” ጋዜጣ በእነ አቶ አየለ ጫሚሶ ከሳሽነት በዛሬው ዕለት አዘጋጁና ም/ዋና አዘጋጁ በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በቁጥጥር ስር እንደዋሉ ለኢትዮጵያ ዛሬ ከአዲስ አበባ የደረሰው ዘገባ ያስረዳል። ከሳሻቸው አቶ አየለ ጫሚሶ መሆናቸው ታውቋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ነገሌ ቦረና በሁለት ሆቴሎች በተወረወሩ ቦምቦች 3ሞቱ፣ 5 ቆሰሉ

Ethiopia Zare (ኀሙስ ግንቦት 21 ቀን 2000 ዓ.ም. May 29, 2008)፦ ኢህአዴግ አዲስ አበባን የተቆጣጠረበትን 17ኛ ዓመት ባከበረበት ረቡዕ ግንቦት 20 ቀን 2000 ዓ.ም. በነገሌ ቦረና ከተማ በሁለት ሆቴሎች ላይ ተወርውሮ በፈነዳ ቦምብ ሦስት ሰዎች ሲሞቱ አምስት ቆሰሉ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአ.አ. ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ከወለጋው ጭፍጨፋ ጋር በተያያዘ ሲጮኹ አመሹ

Ethiopia Zare (ረቡዕ ግንቦት 20 ቀን 2000 ዓ.ም. May 28, 2008)፦ ዛሬ ማምሻውን በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ከምሽቱ አራት ሰዓት ተኩል ገደማ በስድስት ኪሎ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ሲጮሁ ማምሸታቸውን ከአዲስ አበባ የደረሰን ዘገባ ጠቆመ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በኢትዮጵያ የገበያ ሁኔታ አሳሳቢ ሆኗል

  ነጋዴው በጠባቂ መንቀሳቀስ ጀምሯል  

 ብር ከ25 የነበረው አንድ ነጠላ ሻማ ስድስት ብር ገባ  

የመሣሪያ ሽያጭ ተበራክቷል

Ethiopia Zare(ረቡዕ ግንቦት 20 ቀን 2000 ዓ.ም. May 28, 2008)፦ በተለይ በሀገሪቱ ዋና ዋና ከተሞችና የገጠር ከተሞች አካባቢ ዕለት በዕለት የሚታየው የትናንሽና አስፈላጊ ዕቃዎች የዋጋ ጭማሪ ነዋሪዎችንና ነጋዴዎችን እያራራቀ መሆኑን ከኢትዮጵያ የደረሰን መረጃ ጠቆመ። እንደ መረጃው አገላለጽ በመላ ሀገሪቱ የሚታየው የገበያ ዋጋ ጭማሪ በየዕለቱ የሚያድግ ከመሆኑ የተነሳ ነዋሪው ማኅበረሰብ ሊቋቋመው ከማይችለው አዘቅት ውስጥ እየገባ መሆኑን ለማወቅ ችለናል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...