በትግራይ ክልል የኤሌክትሪክ ኃይል ሙሉ ለሙሉ ተቋረጠ

የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች

“የጁንታው ርዝራዦች በኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ላይ በፈጸሙት ጥቃት፤ በመላው ትግራይ የኤሌክትሪክ ኃይል ዳግም ተቋርጧል” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል

ኢዛ (ረቡዕ የካቲት ፲ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. February 17, 2021)፦ በትግራይ ክልል የኤሌክትሪክ ኃይል አገልግሎት ዳግም ሙሉ ለሙሉ መቋረጡ ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አቶ ነብዩ ከትግራይ ብልጽግና ኃላፊነታቸው ተነሱ

አቶ ነብዩን ስሑል ሚካኤል (በግራ) እና አቶ ሃፍታይ ገብረእግዚአብሔር (በቀኝ)

በምትካቸው አቶ ሃፍታይ ገብረእግዚአብሔር ተሹመዋል

ኢዛ (ረቡዕ የካቲት ፲ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. February 17, 2021)፦ የትግራይ ብልጽግና ፓርቲ ከተቋቋመበት ግዜ አንስቶ የፓርቲው ጽሕፈት ቤት ኃላፊ በመኾን ሲያገለግሉ በቆዩት በአቶ ነብዩ ስሑል ሚካኤል ምትክ አዲስ ኃላፊ ተሾመ። የትግራይ ክልል ብልጽግና ጽሕፈት ቤት የመጀመሪያው ኃላፊ በመኾን ሲያገለግሉ የቆዩትን አቶ ነብዩን ተክተው የጽ/ቤት ኃላፊ በመኾን የተሾሙት አቶ ሃፍታይ ገብረእግዚአብሔር መኾናቸው የብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት አስታውቀዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአራት ከፍተኛ የጦር መኮንኖች የወንጀል ምርመራ ተቋረጠ

Ethiopian Federal Police Commission Crime Investigation Bureau (EFPCCIB)

ከእስር የተለቀቁት የወንጀል ተሳትፎአቸው ዝቅተኛ በመኾኑ ነው

ኢዛ (ረቡዕ የካቲት ፲ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. February 17, 2021)፦ በሰሜን ዕዝ ላይ በተሰነዘረው ጥቃት ላይ ተሳትፈዋል ተብለውና በተለያዩ ወንጀሎች ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር የሚገኙ አራት ከፍተኛ የጦር መኮንኖች ላይ ሲያካሒድ የነበረው የወንጀል ምርመራ ማቋረጡን የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ወንጀል ምርመራ ቢሮ አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአሜሪካው ኩባንያ የንግድ ባንክን አዲስ አደረጃጀት ለማዘጋጀት የወጣውን ጨረታ አሸነፈ

Commercial Bank of Ethiopia (CBE) and McKinsey & Company

ባንኩ በስድስት ወር ውስጥ ከ7.4 ቢሊዮን በር በላይ አትርፏል

ኢዛ (ረቡዕ የካቲት ፲ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. February 17, 2021)፦ ማኬንዚ የተባለው የአሜሪካ ኩባንያ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን አጠቃላይ አደረጃጀት ለመቀየር የሚያስችለውን ጥናትና አዲስ መዋቅር ለማዘጋጀት የወጣውን ዓለም አቀፍ ጨረታ ማሸነፉ ተገለጸ። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በስድስት ወር ውስጥ ከ7.4 ቢሊዮን ብር በላይ አተረፍኩ አለ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በሕገወጥ መንገድ የተከማቸው ሁለት ሚሊዮን ጄሪካን ዘይት ለሸማቾች እየተሰራጨ ነው

Palm Oil

ሸሽጎ ያስቀመጠው ማን እንደኾነ እስካኹን አልተገለጸም

ኢዛ (ሰኞ የካቲት ፰ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. February 15, 2021)፦ በአዲስ አበባ በአንድ ግለሰብ መጋዘን ውስጥ በሕገወጥ መንገድ ተከማችቶ የተገኘው ሁለት ሚሊዮን ጄሪካን ፓልም የምግብ ዘይት፤ ሸሽጎ ያስቀመጠው ማን እንደኾነ ሳይታወቅ ለሸማች ማኅበራት እየተሰራጨ መኾኑ ተገጸለ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወለጋ

PM Abiy Ahmed

ወለጋ ለኢትዮጵያ ነፃነት ሕልውና ተምሳሌት መኾኑን ገለጹ

ኢዛ (ሰኞ የካቲት ፰ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. February 15, 2021)፦ “ወለጋ የኦሮሞ ሕዝብና ለኢትዮጵያ ነፃነትህ ሕልውና ተምሳሌት ነው” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኦነግ በምርጫው መሳተፍ አለመሳተፉ አልለየም

Kejela Merdasa (OLF)

የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊው የመሳተፋችን ነገር 50 በመቶ ነው ይላሉ

ኢዛ (ሰኞ የካቲት ፰ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. February 15, 2021)፦ በኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) አመራር አባላት መካከል ያለውን አለመግባባት ለመፍታት የተለያዩ ማጣራቶች ሲያደርጉ መቆየቱ የሚታወስ ቢኾንም፤ ግንባሩ በቀጣዩ ምርጫ (ምርጫ 2013) የመሳተፍ እድል 50 በመቶ መኾኑን የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊው ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኢዜማ የአንድ የምርጫ ወረዳ ሊቀመንበሩ ተገደሉ

Girma Moges Legesse

በተተኮሰባቸው ጥይት ሕይወታቸው ማለፉን ፓርቲው አስታውቋል

ኢዛ (ሰኞ የካቲት ፰ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. February 15, 2021)፦ በቀጣዩ አገራዊ ምርጫ (ምርጫ 2013) በዋናነት ተፎካካሪ እንደሚኾኑ ከሚጠበቁት ተፎካካሪ ፓርቲዎች መካከል አንዱ የኾነው የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) በደብረዘይት (ቢሾፍቱ) ከተማ የአድአ ምርጫ ወረዳ 1 ሊቀመንበሩ እንደተገደለበት አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ