በአዲስ አበባ የሚካሄደው የግብረሰዶማዊያን ስብሰባ ቁጣ ቀስቅሷል

የኃይማኖት አባቶች ድፍረት ይጎላቸዋል ተባለ

"ይህንን በህይወት በማየቴ እጅግ ስሜቴ ተነክቷል" ጋዜጠኛ ሰይፉ መኮነን

ተቃውሟቸው የታይታና ግብዝነት የሞላበት ነው” ተክለሚካኤል አበበ

Ethiopia Zare (አርብ ህዳር 22 ቀን 2004 ዓ.ም. December 2, 2011)፦ በኢትዮጵያ ዋና ከተማ አዲስ አበባ ነገ ቅዳሜ፡ ዲሴምበር 3 በአፍሪካ የግብረ ሰዶማዊያን ቡድን አሰባሳቢነት በጤና ጉዳዮች ላይ በጁፒተር ሆቴል የሚካሄደው ስብሰባ በዚህ ሳምንት በህብረተሰቡ ዘንድ መነጋገሪያ ከመሆኑም በላይ በተለይ የሀይማኖት አባቶች የወሰዱት አቋም ቀድሞም ቁርጠኝነት ያልነበረውና ወላዋይነት የሞላበት መሆኑ ተገለጸ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሱዳን ኢትዮጵያዊውን የፖለቲካ ስደተኛ ለኢህአዴግ አሳልፋ ሰጠች

Ethiopia Zare ( እሁድ ኅዳር 17 ቀን 2004 ዓ.ም. November 27, 2011)፦ የሱዳን መንግስት በበርካታ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች ላይ እስርና እንግልት እያደረሰ ነው በሚል እየተወነጀለ ባለበት በአሁኑ ወቅት አንዷለም አለማየሁ የተባለውን የኢህአዴግ ተቃዋሚ አሳልፎ ለኢትዮጵያ መንግስት እንደሰጠ ከደረሰን ዜና መረዳት ተችሏል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኢትዮጵያ ጦር በድጋሚ ወደ ሶማሊያ ሊዘምት ነው

ፕሬዝዳንቱ አልፈለጉምየሶማሊያ ባለስልጣን

ተጠቃሚው አል-ሻባብ ነውየፖለቲካ ተንታኞች

Ethiopia Zare (ቅዳሜ ኅዳር 9 ቀን 2004 ዓ.ም. November 19, 2011)፦ የሶማሊያ አብዛኛውን ክልል የተቆጣጠረውና ከአልቃይዳ ጋር ቀጥታ ግንኙነት አለው የሚባለውን አል-ሻባብን ለመመንጠር፤ የአፍሪካ ህብረት በድምሩ 10 ሺህ የሚገመት ጦር ለመላክ እየሞከረ ሲሆን የኢትዮጵያን ጦር ተሳትፎ በተመለከተ ግን ካሁኑ አወዛጋቢ አስተያየቶች እየተሰጡ ነው። ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኢሕአዴግ መንግስት ለአምባሳደሩ መታሰር በቂ መልስ አላቀረበም

“የዓለም አቀፍ ህግጋትን ጥሰዋልየስሎቫክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስተር

Ethiopia Zare ( ቅዳሜ ኅዳር 9 ቀን 2004 ዓ.ም. November 19, 2011)፦ አጠያቂ በሆነ መልኩ በኢህአዴግ ታጣቂ የጸጥታ ኃይሎች ተይዘው ለ3 ቀናት በእስር የቆዩትን አምባሳደር በተመለከተ የኢትዮጵያ መንግስት እጅግ ዘግይቶ የሰጠው ምላሽ አጥጋቢ አይደለም ሲሉ የስሎቫክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አወገዙ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አድባር በቶሮንቶ ዩኒቨርስቲ የተሳካ ውይይት አደረገ፡

የመምህር የኔሰው መስዋእትነት ተዘከረ፡ ሁለት ወጣት ምሁራን የጥናት ስራዎች አቀረቡ

Ethiopia Zare (አርብ ኅዳር 8 ቀን 2004 ዓ.ም. November 18, 2011)፦ አድባር በመባል የሚታወቀው የውይይትና ክርክር ክበብ በቶሮንቶ የተሳካ ውይይት ከማድረጋቸውም በላይ ‘ፍትህና ነጻት በሌለበት ሀገር መኖር ሰለቸኝ” በማለት ራሱን በእሳት ያቃጠለው መምህር የኔሰው ገብሬ መስዋእትነት በታላቅ ሁኔታ ተዘከረ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

ጋዜጠኛ አበበ ቶላ (አቤ ቶክቻው) ወደ ኬንያ ተሰደደ

Ethiopia Zare (ሰኞ ኅዳር 4 ቀን 2004 ዓ.ም. November 14, 2011)፦ በአውራምባ ታይም፣ በተለያዩ ጋዜጦችና ድረ ገጾች ላይ ወጋወጎችን በመጻፍ የሚታወቀው ጋዜጠኛ አበበ ቶላ (አቤ ቶክቻው) በደህንነት ሰዎች በደረሰበት ተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያና ክትትል ከሀገሩ ተሰዶ በጎረቤት ሀገር ኬንያ እንደሚገኝ ምንጮች ገለጹ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

እስክንድር ነጋና አንዷለም አራጌ አንድ ላይ በካቴና ታስረው ፍርድ ቤት ቀረቡ

ናትናኤል መኮንን ክፉኛ መደብደቡን ለፍርድ ቤት ገለጸ

Ethiopia Zare (ሐሙስ ጥቅምት 30 ቀን 2004 ዓ.ም. November 10, 2011)፦ ልደታ በሚገኘው በከፍተኛ ፍርድ ቤት ዛሬ የቀረቡት ስምንት ተከሳሾች መካከል ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋና አንዷለም አራጎ አንድ ላይ በካቴና ተጠፍረው መቅረባቸውና የአንድት ፓርቲ ምክር ቤት አባል የሆነው ናትናኤል መኮንን በፖሊሶች ክፉኛ መደብደቡን ለፍርድ ቤቱ ማስረዳቱን የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች ገለጹ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

ወደ እስራኤል የሚሰደዱ ኢትዮጵያዊያን በሲና በረሃ ቀልጠው እየቀሩ ነው

የሰወነት አካላቸው በጥቁር ገበያ ይቸበቸባል

Ethiopia Zare (ቅዳሜ ጥቅምት 25 ቀን 2004 ዓ.ም. November 5, 2011)፦ በግብጽ በኩል አቋርጠው ወደ እስራኤል ሀገር ለመሻገር የሚሞክሩ በርካታ ኢትዮጵያዊያንና ሱዳናዊያን ስደተኞች የሰውነት አካላቸው እየተሰረቀ እሬሳቸው በበረሃ ውስጥ እንደሚጣል ሰብአዊ መብት ተሟጋቾች በመረጃ አረጋገጡ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ቴዲ አፍሮ በፑንትላንድ የሞት ቅጣት ለተወሰነበት ኢትዮጵያዊ 700ሺህ ብር ከፈለ!

Ethiopia Zare ( ቅዳሜ ጥቅምት 18 ቀን 2004 ዓ.ም. October 29፣ 2011)፦ በሶማሊያዋ ፑንትላንድ በጎሳ መሪዎች የሞት ወይንም የ700 ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት ለተወሰነበት አስመሮም ኃይለስላሴ እውቁ የሙዚቃ ሰው ቴዎድሮስ ካሳሁን የገንዘብ ቅጣቱን እንደከፈለለት ተዘገበ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ