”የአንድነትን ሕልውና የመታደግ ጥረታችንን ሕገወጥነት አይገታውም” እነፕ/ር መስፍን

እነኢ/ር ግዛቸው የፓርቲውን የምስክር ወረቀት፣ ጽ/ቤቱን፣ ማሕተሙን፣ ሰነዶችና ንብረቶች እንዲያስረክቡ ተጠየቁ

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ሚያዝያ 19 ቀን 2002 ዓ.ም. April 27, 2010)፦ እነፕ/ር መስፍን የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲን (አንድነትን) ሕጋዊነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት፣ ጽሕፈት ቤቱን፣ ማሕተሙን፣ ሰነዶችና ንብረቶችን እንዲያስረክቧቸው፤ ማሕተሙን እንዳይጠቀሙና እንቅስቃሴአቸውን እንዲያቆሙ ትናንት ለኢንጂንየር ግዛቸው ሽፈራው የፃፉላቸውን ደብዳቤ አልቀበልም ማለታቸውን አስመልክቶ፤ በዛሬው ዕለት ”የአንድነትን ሕልውና የመታደግ ጥረታችንን ሕገወጥነት አይገታውም” በሚል መግለጫ አወጡ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢህአዴግ ፕ/ር በየነ ጴጥሮስን አስጠነቀቀ፤ እርምጃም እወስዳለሁ አለ

Prof. Beyene ፕ/ር በየነ ጴጥሮስEthiopia Zare (ሰኞ ሚያዝያ 18 ቀን 2002 ዓ.ም. April 26, 2010)፦ ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ፤ የመድረኩ ሊቀመንበር ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ ”ሕገ መንግሥቱን የሚፃረርና ኹከት የመፍጠር አዝማሚያ ያለው ንግግር አድርገዋል” በማለት ዛሬ ማምሻውን መግለጫ አወጣባቸው። መግለጫው ”ሕግ የጣሰ ነው” ያለውን የፕ/ሩን ንግግርም ሆነ ወደፊት በሚደረጉ ተመሳሳይ ንግግሮችና መግለጫዎች ላይ እርምጃ እንወስዳለን ይላል። ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኅሊና እስረኞች በገንዘብ ሊተመን የማይችል መስዋዕትነት ከፋዮች መሆናቸው ተገለጠ

Houston, Texasወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳና ሌሎችም ኢትዮጵያዊያን የኅሊና እስረኞች የከፈሉትና በመክፈል ላይ የሚገኙት መስዋዕትነት በገንዘብ ሊተመንና ከቶም ሊካካስ የማይችል መሆኑ ተገለጠ። ይህ የተገለጠው፣ እ.ኤ.አ. ፌብሯሪ 6 ቀን 2010 በአሜሪካ ቴክሳስ ግዛት “ድጋፍና አክብሮት ለኅሊና እስረኞች” በሚል መርኅ በሂዩስተን ከተማ የተከናወነው በኢትዮጵያ የሚገኙ የኅሊና እስረኞች ማሰቢያና ድጋፍ ማሳያ ሥነሥርዓትን ያቀጋጀው ኮሚቴ በሰጠው ማብራሪያ ላይ ነው። ሙሉውን አስነብበኝ ...

በአዲስ አበባ የጥላሁን ገሠሠ ሙት ዓመት መታሰቢያ ለሦስት ቀን ይቆያል

ዶ/ር አርቲስት ጥላሁን ገሠሠ Artist Tilahun Gesseseሙሉ ታሪኩን የያዘ መጽሐፍ ይመረቃል፣ በስሙ አደባባይ ይሰየማል

Ethiopia Zare (ሐሙስ ሚያዝያ 7 ቀን 2002 ዓ.ም. April 15, 2010)፦ የዶ/ር አርቲስት ጥላሁን ገሠሠ አንደኛ የሙት ዓመት ከሚያዝያ 15 ቀን እስከ 17 ድረስ በሚቆይ ልዩ ሥነ-ሥርዓት እንደሚከበር ተገለጸ።  ሙሉውን አስነብበኝ ...

ጠ/ሚ መለስ ማስፈራራታቸውን ቀጥለዋል

“እሳት ለኩሶ በሕፃናት ደም መጫወት አይቻልም” ጠ/ሚ መለስ ዜናዊ

“የሕፃናትን ደም ያፈሰሰው ህወሓት/ኢህአዲግ ነው” ተቃዋሚዎች

Ethiopia Zare (ረቡዕ ሚያዝያ 6 ቀን 2002 ዓ.ም. April 14, 2010)፦ ማክሰኞ ሚያዝያ 5 ቀን 2002 ዓ.ም. ጠ/ሚ መለስ ዜናዊ ፓርላማ ተገኝተው ያቀረቡትን መንግሥታዊ ሪፖርት፣ ተቃዋሚዎች “ተራ ማስታወሻ እና ስድ ንባብ ነው” በማለት አጣጣሉት። ሙሉውን አስነብበኝ ...