መድረክ በመስቀል አደባባይ የጠራው ስብሰባ ተከለከለ

በደብረዘይትና በአዲስ አበባ የመጨረሻ ቅስቀሳውን ያካሂዳል

Ethiopia Zare (ቅዳሜ ግንቦት 7 ቀን 2002 ዓ.ም. May 15, 2010)፦ መድረክ ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 7 ቀን 2002 ዓ.ም. (ግንቦት 7 ቀን 1997 ዓ.ም.ትን በማሰብ) በመስቀል አደባባይ ሊጠራው ያሰበው ህዝባዊ ስብሰባ ሳይሳካ ቀረ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

”የመድረክ አባላት አንድ ፖሊስ ገደሉብኝ” የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን

Ethiopia Zare (እሁድ ግንቦት 1 ቀን 2002 ዓ.ም. May 9, 2010)፦ በዛሬው ዕለት የመንግሥት መገናኛ ብዙኀን የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽንን በመጥቀስ፤ ”በመድረክ ፓርቲ የተደራጁ ሦስት ግለሰቦች አንድ ፖሊስ በአሰቃቂ ሁኔታ በጩቤ ወግተው ገደሉ” በማለት መዘገባቸው ከአዲስ አበባ የደረሰን ዘገባ አስረዳ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

የወዛደሮች ቀን ተከበረ

በማትያስ ከተማ

  • ሞና ሳሊን ብርቱካን ሚደቅሳ እንድትፈታ ጠየቁ
  • የኢትዮጵያን መንግሥት ሥርዓት የለሽነት አጋለጡ

May day 2010, Stockholm, Sweden

Ethiopia Zare (ሰኞ ሚያዝያ 25 ቀን 2002 ዓ.ም. May 3, 2010)፦ ባለፈው ቅዳሜ በስዊድን ዋና ከተማ ስቶክሆልም የዓለም ወዛደሮች ቀን (ሜይ ዴይ) በከፍተኛ ድምቀት ተከብሮ ዋለ። በዚህ የሶሻል ዲሞክራቲክ ፓርቲና የሠራተኛው ማኅበር ባዘጋጁት በዓል ላይ ብዙ ሺህ ህዝብ የተገኘ ሲሆን፤ ኢትዮጵያውያንም የሰልፉ ተካፋይ ነበሩ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢትዮጵያ ውስጥ አውቶቡስ ሊሠራ ነው

Holand Car PLC's Abay carEthiopia Zare (ሐሙስ ሚያዝያ 21 ቀን 2002 ዓ.ም. April 30, 2010)፦ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የቤት መኪና በመገጣጠም የሚታወቀውና ”ሆላንድ ካር” የተሰኘው ኃ.የተ.ኩባንያ፤ ሁለት አይነት የህዝብ ማመላለሻ አውቶቡሶችን ኢትዮጵያ ውስጥ መሥራት ሊጀምር መሆኑን አስታወቀ። አንደኛው 130 ሰዎች የሚጭን ሲሆን፤ ሁለተኛው ደግሞ ባለአንድ ፎቅና 240 ሰዎችን የሚጭን መሆኑን አስታውቋል። ሙሉውን አስነብበኝ ...

”የአንድነትን ሕልውና የመታደግ ጥረታችንን ሕገወጥነት አይገታውም” እነፕ/ር መስፍን

እነኢ/ር ግዛቸው የፓርቲውን የምስክር ወረቀት፣ ጽ/ቤቱን፣ ማሕተሙን፣ ሰነዶችና ንብረቶች እንዲያስረክቡ ተጠየቁ

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ሚያዝያ 19 ቀን 2002 ዓ.ም. April 27, 2010)፦ እነፕ/ር መስፍን የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲን (አንድነትን) ሕጋዊነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት፣ ጽሕፈት ቤቱን፣ ማሕተሙን፣ ሰነዶችና ንብረቶችን እንዲያስረክቧቸው፤ ማሕተሙን እንዳይጠቀሙና እንቅስቃሴአቸውን እንዲያቆሙ ትናንት ለኢንጂንየር ግዛቸው ሽፈራው የፃፉላቸውን ደብዳቤ አልቀበልም ማለታቸውን አስመልክቶ፤ በዛሬው ዕለት ”የአንድነትን ሕልውና የመታደግ ጥረታችንን ሕገወጥነት አይገታውም” በሚል መግለጫ አወጡ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢህአዴግ ፕ/ር በየነ ጴጥሮስን አስጠነቀቀ፤ እርምጃም እወስዳለሁ አለ

Prof. Beyene ፕ/ር በየነ ጴጥሮስEthiopia Zare (ሰኞ ሚያዝያ 18 ቀን 2002 ዓ.ም. April 26, 2010)፦ ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ፤ የመድረኩ ሊቀመንበር ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ ”ሕገ መንግሥቱን የሚፃረርና ኹከት የመፍጠር አዝማሚያ ያለው ንግግር አድርገዋል” በማለት ዛሬ ማምሻውን መግለጫ አወጣባቸው። መግለጫው ”ሕግ የጣሰ ነው” ያለውን የፕ/ሩን ንግግርም ሆነ ወደፊት በሚደረጉ ተመሳሳይ ንግግሮችና መግለጫዎች ላይ እርምጃ እንወስዳለን ይላል። ሙሉውን አስነብበኝ ...