ክርስትና እና ፖለቲካ (ግርማ ካሣ)

ግርማ ካሣ

እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ አደረሳችሁ!

(ይህ መልዕክት የክርስትና እምነት ተከታይ ለሆኑ ኢትዮጵያውያን የተዘጋጀ ነው። ነገር ግን ጌታችን መድኃኒታች ኢየሱስ ክርስቶስ በሙስሊሞች ዘንድም ኢሣ ተብሎ እንደ ታላቅ ነብይ የሚቆጠር ስለሆነ፣ ለሙስሊም ወገኖቼም በተዘዋዋሪ መንገድ ትምህርት ሰጪ ነው ብዬ አስባለሁ።)

የአትላንታ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መጋቢ የሁኑት ቄስ ቶሎሳ ጉዲና ንግግር ያደረጉበት አንድ ታላቅ መንፈሣዊ ስብሰባ በአዲስ አበባ ታላቁ ስቴዲየም ተደርጎ እንደነበረ ሰምቻለሁ። ከስታዲየሙ ትንሽ ሄድ ብሎ በሚገኘው በመስቀል አደባባይ፣ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ወገኖቻችን በተገኙበት፣ የመስቀል በዓልን ምክንያት በማድረግም ከጥቂት ቀናት በፊት፣ አቡነ ፓትሪያክ ጳውሎስ ንግግር አድርገው ቡራኬ ሰጥተዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የግንቦት ሰባት ሌላ የተሳካ ስብሰባ በዳላስ ተካሄደ፡ ሁለት መቶ ሀምሳ ሰው ተጠመቀ

ልጅ ተክሌ

መስከረም 25 መሆኑ ነው? እኛ ተናጋሪዎቹ እኛ እንግዶቹ ወደ ውስጥ ስንገባ፡ የዳላስ ክራውን ፕላዛ ሆቴል የመሰብሰቢያ አዳራሽ ከግማሽ በላይ ሞልቷል። ስብሰባው ከተጠራበት ሰዓት ሰላሳ ደቂቃ በላይ ዘግይተን መጀመር ግን አልፈለግንም። ዶ/ር ብርሀኑ መሀል ቁጭ አለ። አቶ ዘነበ ሀይለማሪያም ገነሜ በስተግራ፡ ልጅ ተክሌ ደግሞ በስተቀኝ ተቀመጠ። የመድረኩ መሪና ሰብሳቢው አቶ አበበ እንግዶቹን አስተዋወቀ። ስብሰባው ተጀመረ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በሲያትል ተደመምን፤ በካልግሪም ኮራን፤ በፖርትላንድም ተደነቅን

አለቃ ተክሌ - ከቫንኩቨር

ሀተታ እና አስተያየት፤ ከቫንኩቨር ንግስ መልስ ወደ ፒስ (ፒትስ) በ(ር)ግ

ሊቀ ዲያቆኑ፤ የሲያትል ህዝብ

ሊቀ ዲያቆን ታደሰ የሲያትሉ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ዲያቆን “ቲኬት ግዙ ምናምን አትበሉን። ትኬታችሁን ያዙ። በእለቱ ብቻ ተዘጋጅታችሁ ጠብቁን” ብሎ ለሲያትል ህዝብ ልንቸበችብ የወሰድነውን ቲኬት ሲመልስብን ትንሽ ደንግጠን ነበር። የበአሉ ጊዜ እያነሰና እያጠረ ደግሞ እየቀነሰ ሲመጣ ሰው ይመጣ ይሆን ብለን ትንሽ ማሰባችን፤ ትንሽም መጠራጠራችን አልቀረም። ልበ ሙሉው ሊቀ ዲያቆን ግን ይገስጸን ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ነፍስና ስጋ፤ ትናንት ለስጋችን ነበር ዛሬ ደግሞ ለነፍሳችን

አለቃ ተክሌ

እነሆ ቅድስት ማርያም በቫንኩቨር ልትከብር ነው

ሰንጋው ተመርጧል፤ ቢላ ተስሏል

ሰንጋው ተመርጧ። ጋሽ ከቤና ሙሌ ናቸው የመረጡት። ጋሽ ከቤ ባለፈው ወደ ዲሲ ለመስከረም 3ቱ ሰልፍ ሊያመራ ሲያኮበኩብ የነበረው ከበደ ሀይለማሪያም ነው። እህቶቻችንና እናቶቻችን እኛን ወንዶቹን ወደምድጃ አናስደርስም ብለው ወገባቸውን አስረው ተነስተዋል። እዚህ ከምእራቡ ዓለም ሁላችንም ጾታችን አንድ እንደሆነ አላወቁም። ወይ ሁላችንም ሴቶች ነን። ወይም ሁላችንም ወንዶች ነን።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

እኛና ጠላት፣ ሰልፍና ሰይፍ፤ ሰይፍ አልመዘዝንም እስኪ ሰልፍ እንውጣ፤ ሴፕቴምበር 13፣ 2009

አለቃ ተክሌ - ቫንኩቨር ካናዳ

ይሄ ፅሁፍ የቅስቀሳ ነው፤ ከጋሽ ከቤ ልጀምር

ቅስቀሳ የማይወድ ከዚህ ሳይዘልቅ ያቁም። ብዙ አይልፋ። እነሆ ቅስቀሳ። አሁን ጥቅምት ሲመጣ 56ኛ ዓመቱን ይይዛል። ያሳዝነኛል። አንዳንደዬ ቢያናድደኝም፤ ሁልግዜ ግን ያስደስተኛል። ከቫንኩቨር ሲያትል ከሲያትል ዲሲ፡ ከዲሲ ቶሮንቶ ከቶሮንቶ ደግሞ መልሶ ካልግሪ ሲንከራተት፡ ጽናቱ ይገርመኛል። ፅድቅን ፍለጋ አይደለም። ሰማያዊ ድህነትን ሽቶም አይደለም። ዝናና ክብርም አይደለም ረሀቡ። የኢትዮጵያ ጉዳይ እያንገበገበው እንጂ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በእውኑ እኛ ከብርቱካን ምን አለን? ብርቱካንስ ከኛ ምን አላት?

አለቃ ተክሌ (ለዓመቱ ታላቅ ሰው ሽልማት ሥነሥርዓት ላይ ቀረበ)

የብርቱ ካህን ፈተናና የብርቱ ካህን የሕይወት ጥሪ

ደሳሳ ጎጆ። ፍቅር። በእበት የተለቀለቀ ወለል። አርበጠባብ አልጋዎች። የልጅ እናት። ብርቱካን፡ ቀድሞውንም፡ በልጅነቷ ካህን እንድትሆን የተጠራች መሆኗና መናገር ይቻላል። የታመሙትን ለማጥናናት፡ የተበደሉትን ለመካስ፡ የተጠቁትን ለመከላከል፡ ተስፋ ያጡትን ተስፋ ለመመገብ፡ ፍትህ ያጡትን ደግሞ ፍትህ ለማደል፡ የተጠራች ካህን። የዛሬ ሶስት ሳምንት አካባባ፡ ዋሽንግተን ዲ.ሲ. ያገኘሁት ሳምሶን ጋዜጠኛ ነው። ወይም ነበር። እኔና ሳምሶን፡ የኬንያን ስደት ለሶስት ዓመታት ባንድ ላይ አርሰነዋል። ገፍተነዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

መኢአድና አንድነት እንዲዋሃዱ የቀረበ ጥሪ (አማኑዔል ዘሠላም)

አማኑዔል ዘሠላም ( This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it. ) ነሐሴ 29 ቀን 2001 ዓ.ም.

“መሪያችን ብርቱካን ሚደቅሳ በግፍ ታስራ፣ ደጋፊዎቻችን በየቦታው ወከባ እየደረሰባቸው፣ በህዝብ ገንዘብ የሚተዳደሩ የመንግሥት መገናኛ ብዙኀን ርካሽ ፕሮፖጋንዳ እየረጩ፣ ስለምርጫ ማሰብና ስለ ምርጫ ማውራት እራስን ማታለል ነው። አንዳች ጥቅም ለማያመጣ ገዢው ፓርቲ በውጭ ሀገር መንግሥታት ለመደገፍ ሲል ብቻ የሚጫወተውን የፖለቲካ ጨዋታ ለማዳመቅ ፍላጎቱ የለንም።” [1]

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ለመስከረም 3 ሰልፍ ጋባዣችን ህሊናችን ነው (ፍቅሩ ይበልጣል)

ፍቅሩ ይበልጣል

መስከረም 3 ቀን 2002 ዓ.ም. (September 13, 2009) በዋሽንግተን ዲ.ሲ. በዋይት ሐውስ ፊት ለፊት 100 ሺህ ዕድምተኛ የሚጠበቅበት እና ወያኔ በህዝባችን ላይ የፈጸማቸውንና በመፈፀም ላይ ያለውን በደል፣ ስቃይ፣ ግድያና እስራት ለማጋለጥ ኢትዮጵያውያንና ሌሎችም ኢትዮጵያንና ህዝቧን የሚወዱ ሁሉ ሊገኙበት የሚገባ ታላቅ ሰልፍ የሚደረግበት ቀን ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሠላማዊ ትግል ሐዋርያው አቶ ስየ አብርሃ (ሄለን ነገራ)

ሄለን ነገራ This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it. 

ሰሞኑን በአዳማ ከተማ የአንድነት ፓርቲ የጠራው ስብሰባ በድንኳን ሰባሪዎች ተገለበጠ ተብሎ የተለያዩ አስተያቶችን እያነበብን ነው። እውነቱን ለመናገር ለኔም ሆነ ለጓደኞቼ ምንም የሚደንቅም የሚያናድድም ዜና አልነበረም። ወያኔም ያንን አስመልክቶ በአቶ በረከት ስምዖን በኩል የተለመደ የውሸት ማስተባበያውን መስጠቱም አልደነቀኝም። ይልቁንም እኔን የገረመኝ ያንን ክስተት አስታከው የቀድሞ የወያኔ ቁንጮ ባለሥልጣን አቶ ስየ አብርሃ የሰጡት መግለጫ (ጽሑፍ) ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የገብረመድህን ወግ - ክፍል ሁለት

የገብረመድህን እንባ፤ ከቀይሽብር እስከ ሀውዜን፡ ከሀውዜን እስከ አሁን

አለቃ ተክሌ - ከቫንኩቨር ካናዳ

 ትንሽ እንደ መግቢያ፡ ትንሽ እንደድልድይ

ከወያኔ ከድቶ ወደናት አገሩ የተቀላቀለውንና የሕወሀትን መሰሪ ተልእኮ ሲያጋልጥ የኖረውን የገብሬን ወግ ጀምሬላችሁ ነበር። ዛሬም የገብሬን እንባ እቀጥላለሁ። ከዚያ በፊት ግን በዚህ በገብሬ ወግ ምክንያት በተሰጡ አስተያየቶች ትዝ ስላሉኝ አንዳንድ ሰዎች ትንሽ ማስታወሻ ላስቀምጥ።